Amharic

36 prayers

~542w BH04959
  • Covenant

አቤቱ አንተ የዘላለም ንጉሥ፣ ብሔረሰቦችን ፈጣሪ፣ እያንዳንዱን ፈራሽ አጥንት ገንቢ የሆንከው ሆይ፣ ክብር ለአንተ ይሁን! ከእነዚያ ከአንተ ከራስህ በስተቀር ከሁሉም ሌላ ነገር ራሳቸውን ከአላቀቁት፣ የገዛ ራሳቸውን ወደ አንተ አቅጣጫ ከመለሱት፣ በአንተ በታዘዙት መከራዎች ወደ ስጦታዎችህ አቅጣጫ ከመዞር ካልተገኙት ጋር እንድትቆጥረኝ፣ የሰው ዘርን በመላ ወደ ግርማህና ወደ ክብርህ አድማስ፣ አገልጋዮችህንም ወደ ፀጋህና ወደ ችሮታዎችህ መንበር በጠራህበት ስምህ እለምንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ፣ የቸርነትህን እጄታ አጥብቄ ይዣለሁ፣ በችሮታህም ካባ ዘርፍ ላይ በጽናት ተንጠላጥዬአለሁ፡፡ ስለዚህ የአንተን ትዝታ በስተቀር የሌላውን የማንኛውንም ሰው ትዝታ ከውስጤ የሚያነፃውን ከቸርነትህ ደመናዎች እንድትልክልኝና ወደ እርሱ የአንተን ቃል-ኪዳን ያፈረሱት፣ በአንተና በምልክቶችህ ያላመኑት ቅዋሜ ቀስቃሾች ሊቃወሙት ወደተሰለፉበት፣ የመላው የሰው ዘር የስግድት ዓላማ ወደሆነው ለመመለስ እንድታስችለኝ እለምንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ በቀናትህ የልብስህን መዓዛዎች፣በገጽህ ብርሃን ውበቶች መከሰቻ ጊዜም የግልጸትህን እስትንፋሶች አትንፈገኝ፤ አንተ የሚያስደስትህን ነገር ለማድረግ ኃይል የተመላህ ነህና፤ ምንም ነገር የአንተን ፈቃድ ሊቋቋም፣ ወይንም አንተ በስልጣንህ የወሰንከውን ሊያስቀር አይችልም፡፡ ከአንተ ከፍጹም ኃያሉ፣ ከፍጹም ጠቢቡ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እርሱ ኃያሉ፣ ይቅር -ባዩ ፣ ሩኅሩኁ ነው፤ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ! አገልጋዮችህን በሲኦልና በስህተት አዘቅት ውስጥ ሆነወው ትመለከታቸዋለህ፣ አቤቱ አንተ የዓለም ፍላጎት ሆይ፣ የመለኮታዊ መርሖ ብርሃንህ ወዴት ነው. አንተ ረዳት ቢስነታቸውንና ደካማነታቸውን ታውቃለህ፤ አንተ የመንግስተ-ሰማይና የምድር ኃይሎች ሁሉ በመዳፉ ውስጥ የሚገኙት ሆይ፣ የአንተ ኃይል ወዴት ነው. ጌታ አምላኬ ሆይ፣ ከእነዚያ በመጽሐፍህ ውስጥ የሚገኙትን ትዕዛዛትህን ከአከበሩት አንዱ እንድሆን ፈቃድህ ይሆን ዘንድ በፍቅራዊ ደግነትህ ብርሃኖች ውበት ፣ በዕውቀትህና በጥበብህ ውቅያኖስም መትመም፣ የመንግስትህን ሕዝቦች በአሳመንክበትም ቃልህ እለምንሃለሁ፡፡ ለታማኞችህ ለእነዚያ የመለኮታዊ ዕውቀት ብልጭታን ወይን -ጠጅ ከቸርነትህ ጽዋ በመጠጣት ፍላጎትህን ለመፈፀምና ቃል-ኪዳንህንና አዲሱን ሥርትህን ለመጠበቅ ፈጥነው ለተነሱት ያዘዝክላቸውን ለእኔም እዘዝልኝ፤ አንተ የፈለግኽውን ለማድረግ ኃይል የተመላህ ነህና፡፡ ከአንተ ከሁሉን አዋቂው ፣ ከፍጹም ጠቢቡ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡
ጌታ ሆይ፣ አቤቱ አንተ የሰዎች ሁሉ ጌታ ሆይ በዚህና በወዲያኛው ዓለም የሚያበለጽገኝንና ወደ አንተ የሚያቀርበኝን በቸርነትህ እዘዝልኝ፡፡ ከአንተ ከአንዱ ከኃያሉ፣ ክብር ከተመላው በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ጌታ ሆይ፣ እርምጃዎቻችንን በመንገድህ ላይ አጠናክርልን፣ ልቦቻችንንም አንተን እንዲታዘዙ አበርታልን፣ ገልፆቻችንን ወደ አንድነትህ ውበት መልስልን፣ ልቦናዎቻችንን በመለኮታዊ አንድነትህ ምልክቶች አስደስትልን፣ የሕያዋን ሁሉ ህልውና በታላቅነትህ ራዕይ ፊትውዳሴህን መዝሙር ይዘምር ዘንድ፣ አካሎቻችንን በፀጋህ መጎናፀፊያ አስጊጥልን፣ ከዓይኖቻችንም ላይ የኃጢአተኛነትን ግርዶሽ ግለጥልን፣ የፀጋህንም ጽዋ ስጠን፡፡ ጌታ ሆይ የፀሎት ቅዱስ የላቀ ሐሴት፣ ከቃላትና ከፊደላት ከፍታ በላይ ከፍ ያለ፣ ከክፍለ -ቃልና ከድምጽ ሁኔታም የመጠቀ ፀሎት -ነፍሶቻችንን ይሞላ ዘንድ፣ ሁሉም ነገሮችም በውበትህ ግልጸት ፊት ፍጹም ወደሌለ- ነገር ይለወጡ ዘንድ፣ ምሕረት በተመላበት ቃላትህና በመለኮታዊ ሕያውነትህ ምስጢር ራስህን ግለጽ፤ ጌታ ሆይ!እነዚህ በቃ ኪዳንህና በአዲስ ሥርዓትህ ጥብቅና ጠንካራ ሆነው የቆዩ፣ የእምነትህን የጽናት ገመድ አጥብቀው የያዙ፣ በታላቅነትህም ካባ ጠርዝ ላይ የተንጠላጠሉ አገልጋዮችህ ናቸው፡፡ ጌታ ሆይ፣ በፀጋህ እርዳቸው በኃይልህም አጠናክራቸው አንተንም እንዲታዘዙ ሽንጦቻቸውን አበርታ፤ አንተ ይቅር ባዩ ፀጋ የተመላው ነህና፤ አቤቱ አንተ ሩህሩህ አምላክ ሆይ! ስለአነቃኽንና እንዳስተውል ስለአደረግኽኝ ምስጋና ለአንተ ይሁን፤ የሚያይ አይን ሰጠኽኝ፤ የሚሰማ ጆሮም ለገስክኝ፣ ወደ መንግስትህ እንድገባ አደረግኽኝ፣ ወደ መንገድህም መራኽኝ ትክክለኛውን መንገድ አሳየኽኝ፣ ወደ መዳኛ መርከብም እንድገባ አደረግኽኝ፣ አምላክ ሆይ! ጽኑ፣ ጠንካራና የማልበገር እንድሆን አድርገኝ፣ ከኃይለኛ ፈተናዎች ጠብቀኝ፣ በኃይል በተጠናከረው የቃል-ኪዳንህና የአዲሱ ሥርዓትህ ምሽግ ውስጥ ከልለህና ጠብቀህ አኑረኝ፡፡ አንተ ኃይል የተመላው ነህ፡፡ አንተ የሚያየው ነህ፤ አንተ ሰሚው ነህ፡፡ አቤቱ አንተ ሩኅሩኁ አምላክ ሆይ፤ እንደመስታወት በፍቅርህ ብርሃን የሚያንፀባርቅ ልብ ስጠኝ፣ ይህን ዓለም በመንፈሳዊ የፀጋ ጎርፎች አማካይነት ወደ ጽጌረዳ አትክልት ስፍራ ለመለወጥ የሚያስችሉኝን አስተሳሰቦች ለግለሰኝ፡፡ አንተ ሩኅሩኁ፣ መሀሪው ነህ፤ አንተ ታላቁ ቸር አምላክ ነህ፤ አቤቱ አንተ ጌታዬና አለኝታዬ ሆይ! ተወዳጆችህ በኃያሉ ቃል-ኪዳንህ ጽኑ እንዲሆኑ ለግልጹ እምነትህ ታማኝ ሆነው እንዲኖሩ፣ በብርሃናት መጽሐፍ ውስጥ ያስፈርካቸውን ትዕዛዛት እንዲፈጽሙ፣ የመርሖ ዓርማዎችና የላይኛው ዓለም ጉባኤ ፋኖሶች ወሰን የሌለው ጥበብህ ምንጮች ከከፍተኛው ሰማይ በማብራት በትክክል የሚመሩ ከዋክብት እንዲሆኑ እርዳቸው፤ በእውነቱ፣ አንተ የማይበገረው ፍጹም ኃያሉ ፍጹም ኃይል የተመላው ነህና፤

bahaiprayers.net
Also in: en lo sm
~367w BH01026
  • Tablet of the Holy Mariner

  • እውነቱን ታውቁ ዘንድ የቅዱሳን መርከበኛ መልዕክት አጥኑ የተባረከው ውበት በመጪው ጊዜ የሚፈፀሙት ድርጊቶች ሙሉ በሙሉ እንደተነበዬ አስተውሉ ፡፡ እነዚያ የሚያስተውሉት ጥንቃቄ ያድርጉ፡፡ እርሱ ፀጋ የተሞላው በጣም ተወዳጅ ነው ቅዱስ መርከበኛ ሆይ የዘለአለም መርከብህን በሰማይ ሰራዊት ፊት እንድትታይ እዘዛት፤ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን፤ በእርሱ ከሁሉም በላይ ድንቅ በሆነው ስም በጥንቱ ባህር ላይ አንሳፍፋት፡፡ ንዑድ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን ፍጹም ከፍተኛ በሆነ አምላክ ስም መልአካዊዎቹ መናፍስት እንዲሳፈሩአት አድርጋቸው፡፡ ንዑድ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን፤ ከዚያም ምናልባት በውስጧ የሚኖሩበት በዘላለማዊው ግዛት ወደደ ሚገኘው ወደ ቅርበት መጠለያ ይደርሱ ዘንድ
    ንዑድ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን በክቡር ውቅያኖስ ላይ እንድትጓዝ ከታሰበችበት እንድትለቀቅ አድርጋት፡፡ ንዑድ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! ቀይማ ባህሮች ዳርቻ ወደ ሆነው ወደ ተቀደሰው ባህር ዳርቻ ከደረሰች በኋላ ንዑድ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን፡፡ በውስጡ ጌታ በሞት አልባ ዛፍ ውስጥ በሁለቱ ነበልባል ወደታዬበት ማዕከል ንዑድ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን በውስጡ የእርሱ እምነት መገለጫዎች እራሳቸውን ከራስ ወዳድነትና ከምድራዊ ብርቱ ስሜት ወዳነፁበት ፤ ንዑድ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን በዙሪያው የሙሴ ክብር ዘላለም ከሚኖረው ሰራዊት ጋር ወደሚዞረው ንዑድ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን ከውስጡ የእግዚአብሔር ልጅ ከታላቅነቱ ጉያ ወደ ተዘረጋበት ፤ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! ለነዋሪዎቹ ሁሉም መለኮታዊ ባሕርያት የተነገሩላቸው ቢሆንም፣ በውስጡ የእምነቱ መርከብ እንቅስቃሴ አልባ ሆና ወዳለችበት ማዕከል፤ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! ከመርከቧ እንዲወርዱና ወደዚህ ወደማይታየው መንግስተ-ሰማያዊ ማዕከል እንዲገቡ እዘዛቸው፤ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! መርከበኛው ሆይ! ለእነዚያ በመርከቧ ውስጥ ለሚገኙት፤ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! ምናልባት እንደበረዶ ነጭ በሆነው በተቀደሰው ሥፍራ እንዳይዘገዩ፤ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! ይልቁንም ጌታ በዝቅተኞቹ ዓለማት ከመጠቀስ ሁሉ በላይ ወዳከበረው ማዕከል በመንፈስ ክንፎች ይበሩ ዘንድ፤ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! ልክ በዘላለማዊ የእንደገና መሰባሰብ ግዛት እንደሚገኙት የተመረጡ አዕዋፋት በህዋ ውስጥ ይከንፉ ዘንድ ፤ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! በብርሃን ባሕሮች ውስጥ የተደበቁትን ምሥጢራት ያውቁ ዘንድ፣ በምሥጢራዊው መጋረጃ በስተኋላ እያለህ ያስተማርንህን አስተምራቸው፡፡ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! እነርሱ የምድራዊ ውስንነቶችን ደረጃዎች አልፈው የመለኮታዊ መርሖ ማዕከል ወደሆነው ወደ መለኮታዊ አንድነቱ ደረጃ ደረሱ፡፡ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! እነርሱ ወደዚያ ጌታ ከእነርሱ ደረጃ በላይ እንዲሆን ወዳዘዘው ክብር ለመውጣት ተመኙ፡፡ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! በዚያን ጊዜ የሚንበለበለው በራሪ ኮከብ ከእነዚያ በእርሱ ቅርበት መንግስት ከሚኖሩት ውስጥ አውጥቶ ጣላቸው፡፡ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! እነርሱ በክብር ከፍታ ላይ ከሚገኘው ከማይታየው አዳራሽ በስተኋላ የታላቁ ድምጽ እንደሚከተለው ሲናገር ሰሙ፤ ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን1 “ እናንት ሞግዚት መላእክት ሆይ” ንዑዱ ጌታዬ የተወደሰ ይሁን! “ የእነዚያ ለመረዳት ሚችሉት አዕምሮወወች ሊገነዘቡት የማይችሉት ከእውነት የራቀ እምነት መርከብ እንቅስቃሴ አልባ ሆና ወደቆመችበት አካባቢ፤

bahaiprayers.net
~396w BB00005ALL
እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ÷ በፀጋህና በቸርነትህ ኃዘኔን አጥፋ በሉዓላዊነትህና በኃይልነትህ ሥቃዬን አስወግድ፣ አምላኬ ሆይ÷ ኃዘን ከየአቅጣጫው በከበበኝ ጊዜ ፊቴን ወደ አንተ ሳቀና ትመለከተኛለህ፡፡ አቤቱ አንተ የፍጡራን ሁሉ ጌታ፣ ለሚታዩና ለማይታዩት ነገሮች ሁሉ ጥላና ከለላ የሆንከው ሆይ! ከእነዚያ ፎቶቻችውን ወደ አንተ ከመመለስ ከቶ ምንም ከማያግዳቸው ጋር ትቆጥረኝ ዘንድ÷ የሰዎችን ልቦችና ነፍሶች በገዛው ስምህ÷ በምሕረትህ ውቅያኖስ ማዕበልና በፀጋህ የቀኑ ኮከብ ድምቀት እማጠንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ÷ በቀናትህ የደረሰብኝን አንተ ትመለከታለህ፡፡ አንተን ለማገልገል ለመነሣትና ባህርያትህን ለማሞገስ የሚያስችለኝ ታዝልኝ ዘንድ በእርሱ የስሞችህ ጎሕና የባህርያትም የንጋት ሥፍራ በሆነው እማጠንሃለሁ፡፡ አንተ በእውነቱ ፍጹም ኃያሉ÷ ከሁሉም በላይ ኃይል የተመላው፣የሰዎችን ሁሉ ፀሎት ሰሚው ነህና፡፡ በመጨረሻም ተግባሬን ሁሉ ትባርክልኝ ከኃጢአቴም ታነፃኝ ፍላጎቴንም ታሟላልኝ ዘንድ በገጽህ ብርሃን እለምንሃለሁ፡፡ አንተ ለስልጣንህና ለገዥነትህ እያንዳንዱ አንደበት የመሰከረልህ እያንዳንዱ የሚገነዘብ ልብ ስለ ግርማህና ስለ ሉዓላዊነትህ ያወቀልህ ነህና፡፡ የጠየቁህን ከምትሰማው መልስም ለመስጠት ከማትቆጠበው ከአንተ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ከእግዚአብሔር በስተቀር ችግርን የሚያስወግድ አለ ወይ? በል፡- ለእግዚአብሔር ምስጋና ይድረሰው! እርሱ አምላክ ነው! ሁሉም አገልጋዮቹ ናቸው፡ ሁሉም በትዕዛዙ ይኖራሉ፤ አቤቱ አንተ በመከራዬ ጊዜ ማረፊያዬ! በጭንቀቴም ጊዜ ጋሻዬና መከታዬ፣ በችግር ጊዜ መጠጊያዬና መሸሻዬ! በብቸኝነቴም ጊዜ ባልደረባዬ! በኃዘኔ ጊዜ መጽናኛዬ! በጓደኛ -ቢነቴም ጊዜ አፍቃሪ ጓደኛዬ! የኃዘኔን ሥቃይ የምርቃት ኃጢአቴንም ይቅር የምትል ጌታ አምላኬ ሆይ! በዚህ በመለኮታዊ አንድነትህ ዘመን የአንተን ፈቃድ ከሚቃወም ነገር ሁሉ እንድትከልለኝ እንከን የሌለብኝና ያልተበከልኩ ሆኜ ፀጋህን ዛፍ ጥላ እንዳልፈልግ እንቅፋት ከሚሆንብኝ ርኩሰት ሁሉ እንድታነፃኝ፣ ሙሉ በሙሉ ወደ አንተ በመዞር በሙሉ ልቤ አዕምሮዬና አንደበቴ በጋለ ስሜት እማፀንሃለሁ፡፡ ጌታ ሆይ በደካማው ላይ ምሕረት ይኑርህ፤ በሽተኛውንም ፈውስ፣ የሚያቃጥለውንም ጥም አርካ፡፡ የፍቅርህ እሳት የሚጋጋበትን ልብ ደስ አሰኘው፣በመንግስተ ሰማያዊ ፍቅርህና መንፈስህ ነበልባል አንድደው፡፡ የመለኮታዊ አንድነት መቅደሶችን በቅድስና ካባ አጎናጽፋቸው ፣የቸርነትህንም ዘውድ በራሴ ላይ ድፋልኝ፡፡ ፊቴን በፀጋህ ሉል ብርሃን አብራልኝ፣ በቅድስናህም ደጀሰላም አገልግሎት ዘንድ በቸርነትህ እርዳኝ፡፡ ልቤ ለፍጡራንህ በሚኖረው ፍቅር እንዲጥለቀለቅ አድርገው፣የምህረትህ ምልክት፣ የፀጋህ መታወቂያ፣በተወዳጆችህ መካከል ስምምነት አስፋፊ፣ ለአንተ ያደርኩ፣ ያንተን ትዝታ የማወሳ፣ ራሴንም ረስቼ ያንተ የሆነውን ሁሉ የማስታወስ እንድሆን ፈቃድህ ይሁን፡፡ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፣ የይቅርታህንና የፀጋህን ልዝብ ነፋስ አታርቅብኝ፣ ከረዳትነትህና ከፍቅርህ ምንጭ አትንሳኝ፤ በጠባቂ ክንፎችህ ጥላ ሥራ እንዳርፍ ፍቀድልኝ፣ የፍጹም ጠባቂ አይንህን እይታ አሳርፍብኝ፡፡ ስምህን በሕዝብህ መካከል እንዳወድስ፣ ድምጼም በታላላቅ ጉባኤዎች ላይ ከፍ እንዲል፣ ከከናፍሮቼም የአንተ ምስጋና ጎርፍ እንዲፈስ ምላሴን አፍታታ፡፡ አንተ በእውነቱ፣ ፀጋ-የተመላው የተመሰገነው፣ ኃያሉ፣ ምንም የማይሳነው ነህና! ጌታዬ ተወዳጄ፣ ፍላጎቴ ሆይ! በብቸኝነቴ ጊዜ ተጎዳኘኝ በግዞቴም ጊዜ አብረኽት ሁን፤ ኃዘኔን አስወግድልኝ፣ ለውበትህም ያደርኩ አድርገኝ፣ ከአንተ በስተቀር ከሌላው ነገር ሁሉ አግልለኝ፣ በቅድስናህም መዓዛ ወደ አንተ ሳበኝ፡፡ በመንግስትህም ውስጥ ውሎዬን ከእነዚያ ከአንተ በስተቀር ከሌላው ነገር ሁሉ ከተላቀቁት፤ የአንተንም ቅዱስ ደጀሰላም ለማገልገል ከሚናፍቁትና በእምነትህ ከፀኑት ጋር እንድጎዳኝ አድርገኝ፤ ለመልካም ፈቃድህ ከበቁት ሴት አገልጋዮችህ አንዷ ለመሆን አስችለኝ፡፡ በእውነቱ አንተ ፀጋ የተመላው ለጋሱ ነህና፡፡
bahaiprayers.net
Also in: be
~121w AB00553
(በሴት የሚደረግ) እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ! ከሁሉ ነገሮች የማላቀቅንጽዋ ሙላልኝ፣ በአንተ ውበቶችና ስጦታዎች ጉባኤም ውስጥ አንተን በማፍቀር ወይን ጠጅ አስደስተኝ፤ ከክፉ ስሜትና ፍላጎት ወረራዎች ነፃ አውጣኝ፤ የዚህ የሙታን ዓለምን ሰንሰለቶች ከላዬ በጣጥስልኝ፣ በላቀ ሐሴት ወደ ላቀው መንፈሳዊ ዓለም ሳበኝ፣ በሴት አገልጋዮችም መካከል በቅዱስነትህ እስትንፋሶች አድሰኝ፡፡ ጌታ ሆይ ፊቴን በስጦታዎችህ ብርሃኖች አብራልኝ፣ አይኖቼን ፍጹም ድል አድራጊ የሆነውን ኃያልነትህን ምልክቶች ብርሃን በማየት እንዲበሩ አድርግልኝ፤ አቤቱ አንተ የዚህ ዓለምና የላይኛው መንግስት ንጉሴ ሆይ አቤቱ፣አንተ የስልጣንና የኃይል ጌታ ሆይ የአንተን ምልክቶችና ስጦታዎች በሰፊው ለማሰራጨት እምነትህን ለማወጅ፣ ትምህርቶችህን ለማስፋፋት ሕግህን ለማገልገል ቃልህንም ከፍ ከፍ ለማድረግ እችል ዘንድ፣ ልቤን ሁሉን ነገሮች በሚያቅፈው ዕውቀትህ ክብር አስደስትልኝ፣ ነፍሴም በነፍስ ላይ አዲስ ሕይወት በሚዘሩት የታላቅ ሐሴት አስደሳች ዜናዎች እንድትደሰት አድርጋት፤ አንተ በእውነቱ ኃይል የተመላው፣ ዘላለም ሰጪው ሁሉን ቻዩ፣ ምን የማይሳነው ነህ፡፡
bahaiprayers.net
~232w BH09085

*ሟች ወንድ ከሆነ፤

አምላኬ ሆይ ! ይህ በአንተና በምልክቶችህ ያመነ ከአንተ በቀር ከሁሉም ሙሉ በሙሉ የተላቀቀና ፊቱን ወደ አንተ የመለሰ አገልጋይህና የአገልጋይህምልጅ ነው፡፡ አንተ በእውነቱ ምሕረትን ከሚያደርጉት ሁሉ በላይ መሐሪው ነህ፡፡ አቤቱ አንተ የሰዎችን ኃጢአት ቅር የምትልና ስሕተቶቻቸውን የምትሸፍን አምላክ ሆይ፣ከቸርነትህ ሰማይና ከፀጋህ ውቅያኖስ የሚጠበቀውን አድርግለት ከምድርና ከሰማይ መፈጠር በፊት ጀምሮ ወደነበረው የላቀ ምሕረትህ ቅጥር ግቢ ውስጥ እንዲገባ ፈቃድህ ይሁን፡፡ ከአንተ ከዘለዓለም ይቅር ባዩ ከሁሉም በላይ ለጋሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የለምና፡፡ *ሟች ሴት ከሆነች አምላኬ ሆይ! ይህቺ በአንተና በምልክቶችህ ያመነች፣ ከአንተ በቀር ከሁሉም ሙሉ በሙሉ የተላቀቀችና ፊቷን ወደ አንተ የመለሰች ሴት አገልጋይህና የሴት አገልጋይህም ልጅ ናት፡፡ አንተ በእውነቱ ምሕረትን ከሚያደርጉት ሁሉ በላይ መሐሪው ነህ፤ አቤቱ አንተ የሰዎችን ኃጢአት ይቅር የምትልና ስሕተቶቻቸውን የምትሸፍን አምላክ ሆይ ከቸርነትህ ሰማይና ከፀጋህ ውቅያኖስ የሚጠበቀውን አድርግላት፤ ከምድርና ከሰማይ መፈጠር በፊት ጀምሮ ወደነበረው የላቀ ምህረትህ ቅጥር ግቢ ውስጥ እንድትገባ ፈቃድህ ይሁን፤ ከአንተ ከዘላለም ይቅር-ባዩ ከሁሉም በላይ ለጋሱ በስተቀር ለተላ አምላክ የለምና፤

*ከሁለቱ ፀሎቶች ለሟች ፆታ የሚስማማውን ይድገም፡፡ ከዚህም በኋላ አላህ ኡ አብሃ የሚለውን ሰላም ከሚከተሉት ስድስት ትቅሶች ከእያንዳንዳቸው በፊት አንዳንድ ጊዜ ማለትም(በድምሩ ስድስት ጊዜ) በመድገም ጥቅሶቹን እያንዳንዳቸውን አሥራ ዘጠኝ ጊዜ በሚከተለው ቅደም ተከተል ይድገም፡፡

አላህ-ኡ-አብሃ (አንድ ጊዜ) በእውነቱ፡ ሁላችንም እግዚአብሔርን እናመልካለን፡፡ (19 ጊዜ) አላህ-ኡ አብሃ (አንድ ጊዜ) በእውነቱ ሁላችንም በእግዚአብሔር ፊት እንሰግዳለን፡፡ (19 ጊዜ) አላህ-ኡ- አብሃ (አንድ ጊዜ) በእውነቱ፡ ሁላችንም ህይወታችንን ለአምላክ ሰጥተናል፡(19 ጊዜ) አላህ-ኡ-አብሃ(አንድ ጊዜ) በእውነቱ ፡ ሁላችንም አምላክን እናወድሳለን፡፡ (19ጊዜ) አላህ-ኡ-አብሃ(አንድ ጊዜ) በእውነቱ፣ ሁላችንም ለእግዚአብሔር ምስጋና እናቀርባለን፡፡(19 ጊዜ) አላህ-ኡ-አብሃ (አንድ ጊዜ) በእውነቱ፡ ሁላችንም በአምላክ እንታገሣለን፡፡ (19 ጊዜ)

bahaiprayers.net
~1089w BH0870
  • Long Healing

እርሱ ፈዋሹ፣ አርኪው ረዳቱ ፍጹም መሐሪው ነው፡፡ አንተን እጠራለሁ አቤቱ የተከበረው ሆይ፣ ታማኙ ሆይ፣ክብር የተመላው ሆይ! አንተ አርኪው፣ አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው ፤ አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ወደር የሌለው ዘለዓለማዊው ሆይ፣ አንድዬው ሆይ! አንተ አርኪው፣ አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ከሁሉም በላይ የተወደሰው ሆይ፣ ቅዱስ ሆይ አጋዡ ሆይ፣ አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ፣ አንተን እጠራለሁ አቤቱ ወደር የሌለው ሆይ፣ ዘለዓለማዊው ሆይ፣ አንድዬው ሆይ! አንተ አርኪው፣ አንተ ፈዋሹ፣ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ከሁሉም በላይ የተወደሰው ሆይ ቅዱሱ ሆይ፣ አጋዡ ሆይ ፣ አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ሁሉን አዋቂው ሆይ ፍጹም ጠቢቡ ሆይ፣ ከሁሉም በላይ ታላቁ ሆይ፤ አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነወሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ! አቤቱ ሉዓላዊው ሆይ፣ ከፍ አድራጊው ሆይ ፈራጁ ሆይ አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ፣ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ወደር የሌለው ሆይ፣ ዘለዓለማዊው ሆይ ፣ አንድዬው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ ፣ አንተ ነዋሪው ፣ አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ከሁሉም በላይ የተወደሰው ሆይ፣ ቅዱስ ሆይ አጋዡ ሆይ፣ አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ፣ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ተወዳጁ ሆይ፣ ክቡሩ ሆይ፤ ከሁሉም በላይ ደስተኛው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ከሁሉም በላይ ኃያሉ ሆይ፣ አነዋሪው ሆይ ምንም የማይሳነው ሆይ! አንተ አርኪው ፣ አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ!
አንተን እጠራለሁ አቤቱ ገዥው ሆይ፣ በገዛ ራሱ ነዋው ሆይ፣ ሁሉን አዋቂው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ መንፈስ ሆይ፣ ብርሃን ሆይ፣ ከሁሉ በላይ ግልጹ ሆይ አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ በሁሉ የምትዘወትረው ሆይ፣ አንተ በሁሉም የምትታወቀው ሆይ አንተ ከሁሉም ስውር የሆንከው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ፣ አንተ ነዋሪው ፣ አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ድብቁ ሆይ፣ ድል አድራጊው ሆይ፣ ለጋሱ ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ፍጹም ኃያሉ ሆይ፣ ረዳቱ ሆይ ሰዋሪው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ሰሪው ሆይ አርኪው ሆ፣ ነቃዬ ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አስነሺው ሆይ ሰብሳቢው ሆይ፣ ከፍ አድራጊው ሆይ አንተ አርኪው፣ አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ፍጹም የምታደርገው ሆይ፣ የማይገታው ሆይ፣ ፀጋ ተመላው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ቸሩ ሆይ ከልካዩ ሆይ፣ ፈጣሪው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ ትክክለኛው ሆይ ፣ ፀጋ የተመላው ሆይ፣ ለጋሱ ሆይ አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋወው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ ሁሉን አስገዳጁ ሆይ ዘላለም ነዋሪው ሆይ ከሁሉም በላይ አዋቂው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ እጹብ ድንቁ ሆይ! ቀናት ቀደምቱ ሆይ ቸሩ ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ የማደፈረው ሆይ የሐሴት ጌታ ሆይ፣ ተናፋቂው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋው አቤቱ አንተ ነዋው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ ለሁሉ ደጉ ሆይ፣ ለሁ ሩኅሩኁ ሆይ ከሁሉም በላ በጎ አድራጊው ሆይ! አንተ አርኪው፣ አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ለሁሉ አለኝታ ሆይ፤ ለሁሉ መጠለያ ሆይ ሁሉን ጠብቆ አኑዋሪው ሆይ! አንተ አርኪው፣ አንተን እጠራለሁ አቤቱ ለሁሉ አለኝታ ሆይ፣ ለሁሉ መጠለያ ሆይ፣ ሁሉን ጠብቆ አኑዋሪው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ የሁሉ ረዳት ሆይ አንተ በሁሉም ተለማኜ ሆይ ህይወት ሰጪው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱአንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ገላጩ ሆይ፣ አፈራራሹ ሆይ ከሁሉን በላይ መሐሪው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተነዋው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ የሁሉ ረዳት ሆይ፣ አንተ በሁሉም ተለማኜ ሆይ፣ ህይወት ሰጪው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ገላጩ ሆይ፣ አፈራራሹ ሆይ ከሁሉም በላይ መሐሪው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው፣ አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ ነፍሴ ሆይ፤ አንተን የኔ ተወዳጅ ሆይ፣ አንተ እምነቴ ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ ፣ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ጥማትን አርኪው ሆይ፣ ከሁሉም የላቀው ጌታ ሆይ፣ ከሁሉ በላይ ብርቁ ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ ፣ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ ከሁሉ በላይ ታላቁ ትውስታ ሆይ፣ ከሁሉ በላይ ቅዱሱ ስም ሆይ ከሁሉ በላይ ጥንታዊው መንገድ ሆይ አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው፣ አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ ከሁሉም በላ የተወደሰው ሆይ፣ ከሁሉም በላይ ቅዱሱ ሆይ! ብሩኩ ሆይ አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ለኳሹ ሆይ፣ ብሩህ አድራጊው ሆይ፣ ደስታ እምጪው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው ፣ አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ የበረከት ጌታ ሆ! ከሁሉ በላይ ሩኅሩኁ ሆይ ከሁሉም በላይ መሀሪው ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ የማይለወጠው ሆይ ህይወት ሰጪው ሆይ፣ የሕያው ሁሉ ምንጭ ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ፣ አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ሁሉን ነገሮች ጠልቀህ የምታውቀው ሆይ፣ ሁሉን የምታየው አምላክ ሆይ፣ የልሳን ጌታ ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ ግልጽ ሆኖም ስውር የማይታየው ሆኖም ተዋቂው ሆይ፣ በሁሉም የሚፈለገው ተመልካች ሆይ! አንተ አርኪው አንተ ፈዋሹ አንተ ነዋሪው፣ አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አንተን እጠራለሁ አቤቱ አንተ አፍቃሪዎችን የምትሰዋው ሆይ፤ ለክፉዎች የፀጋ አምላክ ሆይ! አርኪው ሆይ፣ እጠራሃለሁ አርኪው ሆይ! ፈዋሹ ሆይ፣ እጠራለሁ ፈዋሹ ሆይ! ነዋሪው ሆይ፣ እጠራሃለሁ ነዋሪው ሆይ! አንተ ዘለዓለም ነዋሪው፣ አቤቱ አንተ ነዋሪው ሆይ! አምላኬ ሆይ ፣ አንተ የተቀደስክ ነህ1 የልግስናህና የፀጋህ በሮች በሰፊው በተከፈቱበትና የቅድስናህ መቅደስ በዘለዓለም ዙፋን ላይ በተተከለበት ቸርነትህ፤ የተፈጠሩትን ነገሮች ሁሉ ወደ አንተ ልግስናዎችና ስጦታዎች ገበታ በጠራህበት ምሕረትህ፣ ሉዓላዊነትህና ታላቅነትህም ተገልፆ በቆመበት ሰዓትና የግዛትህ ኃያልነት እንዲገለጽ በተደረገባት የንጋት ጊዜ አዎን በሚለው ቃልህ በሰማይና በምድር በሚገኙት ሁሉ ፈንታ በገዛ ራስህ መልስ በሰጠህበት ፀጋህ እማጠንሃለሁ፡፡ እንደገናም ይህን የተባረከውን መልዕክት የያዘውን የሚደግመውን፣ መልዕክቱ ጋ የሚደርሰውንም መልዕክቱ በሚገኝበት ቤት አካባቢ የሚያልፈውንም ሁሉ እንድትጠብቅ፣ በእነዚህ ከሁሉም በላይ ውብ በሆኑት ስሞች፣ በእነዚህ ከሁሉም በላይ የተከበሩ እና ከሁሉም በላይ የላቁ ባህሪያት ከሁሉ በላይ በተከበረው ትውስታህ በንጹህና ምንም ጉድፍ በማይገኝበት ውበትህ ከሁሉም በላይ ህቡዕ በሆነው አዳራሽህ ውስጥ በተደበቀው ብርሃንና በእያንዳንዱ ንጋትና ምሽት የመከራን ካባ ባጠለቀው ስምህ እማፀንሃለሁ፡፡ እንግዲህ በዚህ መልዕክት አማካኝነት እያንዳንዱን ህመምተኛ በሽተኛውንና ምስኪኑን ከእያንዳንዱ መከራና ጭንቀት ከእያንዳንዱ አስከፊ ስቃይና ሀዘን አንፃው በዚሁም መልዕክት ወደ መመሪያ መንገዶች ወደ ይቅርባይነትህና ወደ ፀጋህም ጎዳናዎች ለመግባት የሚሻውን ማንኛውም ሰው ምራው፡፡
አንተ በእውነቱ አያል የተመላው ፍጹም አርኪው ፈዋሹ፣ ጠባቂው ፣ሰጪው፣ሩህሩህ ፍጹም ለጋሽ፣ ፍጹም መሐሪ ነህና ፤

bahaiprayers.net
Also in: en is
~303w BH09207
  • Spiritual Qualities

በል፣ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ! ራሴን በፍትሕ ዘውድ፣ አካሌንም በትክክለኝነት ጌጥ አጎናጽፈው፣ አንተ በእውነቱ የስጦታዎችና የበረከቶች ባለቤት ነህና፤ አቤቱ ጌታዬ ሆይ! ውበትህ ህብስቴ የአንተ ቅርበት ብርሃንም ጽዋዬ የአንተም ፍላጎት ተስፋዬ አንተን ማወደስም ሥራዬ አንተን ማስታወስም ባልደረባዬ፣ የአንተ ሉዓላዊነትም እርዳታዬ የአንተ መኖሪያ ስፍራም መኖሪያ ቦታዬ ልክ በግርዶሽ እንደተከለሉ ከአንተ ከተዘጉት ሰዎች ገደቦች በላይ ከፍ ያደረግኽው መኖሪያ ሥፍራም መኖሪያ ቤቴ እንዲሆንልኝ ፈቃድህ ይሁን፡፡ በአውነቱ አንተ የስልጣን፣ የብርታትና የክብር አምላክ ነህና፤ አምላኬ ሆይ፣ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ፣ አለኝታዬ ሆይ፣ የተረጋጋ ኅሊናዬንም በውስጤ አድስ! ከሁሉም በላይ ተወዳጄ ሆይ በኃይል መንፈስ ከእምነትህ ጋር አቆራኘኝ፤ የልቤ ዓላማ ሆይ፣ በክብርህም ብርሃን መንገድህን ግለጽልኝ፡፡ የሕይወቴ ምንጭ ሆይ ፍጹም በላቀው ኃያልነትህ ስልጣን ወደ ቅድስናህ ሰማይ ከፍ አድርገኝ፡፡ አንተ አምላኬ የሆንክ ሆይ፤ በዘለዓለማዊነትህም ልዝብ ነፋስ ሐሴትን ስጠኝ! ባልደረባዬ ሆይ ፣ ዘለዓለማዊ የዜማህ ቃናዎች ሰላምን ያውርዱልኝ፤ ጌታዬ ሆይ፣ የጥንታዊ ገጽህ በረከቶችም ከአንተ በስተቀር ከሌላው ነገር ሁሉ ይጠብቁኝ፤ አቤቱ አንተ የግልጽ ፍጹም ግልጽ፣ የስውር ፍጹም ሥውር የሆንክ ሆይ፣ የማይበላሸው የመለኮታዊ ሕላዌህ ግልፀት የምስራች ሐሴትን ያምጣልኝ፡፡ አምላክ ሆይ፣ ለሰው ዘር ላሳየኽው ፍቅር ክብር ላንተ ይሁን! አቤቱ አንተ ህይወታችንና ብርሃናችን የሆንክ ሆይ፤ አገልጋዮችህን በመንገድህ ምራቸው በአንተም እንድንበለፅግ አድርገን፣ ከአንተም በስተቀር ከሌለው ነገር ሁሉ አንፃን፡፡ አምላክ ሆይ፣ አንተን እንጂ ሌላውን ነገር እንዳናይ ስለአንድነትህ አስተምረን፤ ስለ አንድነትህም ግንዛቤን ስጠን፡፡ አንተ መሐሪውና ፀጋ ሰጪው ነህና፡፡ አምላክ ሆይ፣ የአንተን በስተቀር የእያንዳንዱን ሌላ ነገር ሀሳብ እንዲያጋይ በተወዳጆችህ ልቦች የፍቅርህን እሳት አቀጣጥል፡፡ አምላክ ሆይ፣ ከእምቅድመ ዓለም የነበርክ እስከ ዘለዓለምም የምትኖር መሆንህና ከአንተም በስተቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ እንገነዘብ ዘንድ የተከበረ ዘለዓለማዊነትህን ግለጽልን፤ በእውነት በአንተ ምቾትንና ጥንካሬን እናገኛለን፡፡ እነዚያን ከትክክለኛ መንገድ ወደ ስሕተት መንገድ የተመሩትን ትክክለኞችና የማያዳሉ እንዲሆኑ፣ ደንታቢስ የሆኑበትን እንዲገነዘቡ በፀጋው እንዲረዳቸው እግዚአብሄርን እንለምነዋለን፡፡ እርሱ በእውነቱ ፍጹም ፀጋ የተመላው ከሁሉም በላይ ለጋሱ ነው፡፡ ጌታዬ ሆይ ፣አገልጋዮችህን ከፀጋህ በር አትከልክላቸው፣ ከቅርበትህም መንበር አታርቃቸው፡፡ የአጉል እምነትን ጭጋግ እንዲያስወግዱ፣ የከንቱ አስተሳሰብንና የከንቱ ምኖትን ግርዶሽ ቀዳደው እንዲጥሉ በፀጋህ እርዳቸው፡፡ አንተ በእውነቱ ሁሉ ነገር ያለው፣ ከሁሉ በላይ ከፍተኛው ነህ፤ ከአንተ ከፍጹም ኃያሉ፣ ፀጋ ከተመላው በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡

bahaiprayers.net
Also in: ny hr en ja ky ko no ru sm sw te
~376w ABU0095KIN
  • Spiritual Qualities *(በሴት የሚደረግ) አቤቱ ጌታዬ ሆይ! እኔ አከንተ ሴት አገልጋዮች መካከል አንዷ ነኝ፡፡ ፊቴን ፀጋ ወደተመላበት ችሮታዎችህ ክልልና ወደሚመለከተው የክብርህ መቅደስ መልሼአለሁ፡፡ ውበትህን በማሰላሰል እንድደሰት ከፍጡሮችህ መካከል ከማንኛውም ጋር በአጉል ቁራኛነት ከመጣበቅ ሁሉ እንድላቀቅ፤ በእያንዳንዷም ቅጽበት “ የዓለማት ጌታ የሆነው አምላክ የተወደሰ ይሁን” በማለት እንዳውጅ፣ የአንተ ካልሆነው ነገር ሁሉ አንፃኝ፣ አንተንም እንዳፈቅርና ፍላጎትህን ለማሟላት እንድችል አበርታኝ፡፡ አቤቱ ጌታዬ ሆይ! ውበትህ ህብስቴ፣ የአንተ ቅርበት ብርሃንም ጽዋዬ፤ የአንተም ፍላጎት ተስፋዬ አንተን ማወደስም ስራዬ፣ አንተን ማስታወስም ባልደረባዬ፣ የአንተ ሉዓላዊነትም እርዳታዬ፣ የአንተ መኖሪያ ሥፍራም መኖሪያ ቦታዬ ልክ በግርዶሽ እንደተከለሉ ከአንተ ከተዘጉት ሰዎች ገደቦች በላይ ከፍ ያደረግኽው መኖሪያ ሥፍራም መኖሪያ ቤቴ እንዲሆልንኝ ፈቃድህ ይሁን፡፡ በእውነቱ አንተ የስልጣን÷ የብርታትና የክብር አምላክ ነህና፡፡ አቤቱ አንተ የአገሮች ፈጣሪና የዘለዓለም ንጉሥ የሆንከው ሆይ÷ ሴት አገልጋዮችህን በአንተ የክብረ ንጽህና መቅደስ ውስጥ እንድትጠብቃቸው÷ እነዚያን ለቀናትህ ብቁ ያልሆኑትን አይነት አድራጎታቸውንም ይቅር እንድታለቸው እማፀናለሁ፡፡ አማልኬ ሆጥ ጥርጣሬዎችንና ከንቱ አስተሳሰቦችን ከእነሱ አንፃ፡፡ አቤቱ አንተ የስሞች ሁሉ ጌታና የንግግር ምንጭ ተገቢ ካልሆኑት ከማናቸውም ነገሮች ቀድሳቸው፡፡ አንተ የመላው ፍጥረት ግዛት በመዳፍህ ውስጥ ያለው ነህና፡፡ ከአንተ ከፍጹም ኃይሉ ከሁሉም በላይ ከተከበረው ከንዑድ በገዛ ራሱ ከሚኖረው በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ አምላክ ሆይ! መንፈሴን አድስልኝ፣ አስደስትልኝም ልቤን አንፃልኝ፡፡ አዕምሮዬን አብራልኝ፡፡ ጉዳዮቼን ሁሉ በአንተ ላይ ጥዬአለሁ፡፡ አንተ መሪዬና መሸሻዬ ነህ፡፡ ከእንግዲህ ወዲያ የተከፋሁና ኃዘንተኛ አልሆንም፣ ደስተኛና በሐሴት የተመላሁ እሆናለሁ፡፡ አምላክ ሆይ፤ ከእንግዲህ ወዲያ በሥጋት ውስጥ አልዋኝም፣ ችግርም እንዲያስጨንቀኝ መንገድ አልሰጥም፤ ደስ በማያሰኝ የህይወት ነገር ውስጥ አልኖርም፡፡ አምላክ ሆይ! አንተ ከራሴ ይልቅ ለኔ ትራራልኛለህ፡፡ ጌታ ሆይ፣ ራሴን ለአንተ አደራ ሰጥቻለሁ፡፡ አቤቱ አንተ ሩኅሩህ አምላክ ሆይ፣ አንተ ከራሴ ይልቅ ትራራልኛለህ፡፡ ፍቅርህም በጣም ከፍተኛና እምቅድመ ዓለማዊ ነው፡፡ የአንተን በረከት ባስታወስኩ ጊዜ ደስተኛና ባለተስፋ ነኝ፡፡ በምበሳጭበት ጊዜ የልብና የነፍስ ዕረፍት አገኛለሁ፡፡ በምታመምበት ጊዜ ዘለዓለማዊ ጤንነት ይኖረኛል፡፡ እምነቴን በማጓድልበት ጊዜ ታማኝ እሆናለሁ፡፡ ተስፋ ቢስ በምሆንበት ጊዜ ተስፋ ይኖረኛል፡፡ አቤቱ አንተ የመንግስቱ ጌታ ሆይ! ልቤን ደስ አሰኝልኝ፡፡ ደካማ መንፈሴን በአርታልኝ፡፡ የቆረቆዙ ጅማቶቼንም አጠንክርልኝ፣ አይኖቼንም አብራልኝ፣የመንግስትህን ዜማ እንድሰማና ዘለዓለማዊ ተድላና ደስታ እንዳገኝ ጆሮዎቼን አንቃልኝ፡፡ በእውነቱ፣ አንተ ቸሩ ሰጪውና ሩኅሩኁ ነህና፡፡ አቤቱ የተከበርክ ጌታዬ ሆይ! አንተን ለማገልገልና ቃልህንም ለማስተማር እበቃ ዘንድ፣ ከማንኛውም ህገወጥ ዝንባሌ እንድታቀብ፣ ማንኛውንም አመፀኛ ስሜት እንዳሸንፍ፣ የምግባሬንም ዓላማ እንዳነፃ፣ ምንም ትንኮሳ በማይረብሸው ትሑትነት፣ ምንም ስቃይ በማይበግረው ትዕግስት ምንም ራስ ወዳድነት በማያናውጠው ሐቀኛነት እንድኖር እርዳኝ፡፡ አቤቱ አንተ ሩኅሩኁ አምላክ ሆይ! እንደ መስታወት በፍቅርህ ብርሃን የሚያንፀባርቅ ልብ ፍጠርልኝ፡፡ ይህን ዓለም በመነፍሳዊ የፀጋ ጎርፎች አማካይነት ወደ ጽጌረዳ አትክልት ሥፍራ ለመለወጥ የሚያስችሉኝን አስተሳሰቦች ለግሰኝ፡፡ አንተ ሩኅሩኁ ፣መሐሪው ነህና! አንተ ታላቁ ቸር አምላክ ነህና፡፡
bahaiprayers.net
~73w AB00122
  • Contributions

የእግዚአብሔር ወዳጆች ሁሉ፣ የሚሰጡት ምንም ያህል ትንሽ ቢሆንም እንኳ፣ የሚችሉትን ያህል ማዋጣት አለባቸው፣ እግዚአብሔር ማንኛዋንም ነፍስ ከአቅሟ በላይ አይፈልግባትም፡፡ እንዲህ ያለው መዋጮ ከሁሉም ማዕከሎችና ከሁሉም ምዕመናን መምጣት አለበት፤ የእግዚአብሔር ወዳጆች ሆይ ለእነዚህ ለምታዋጡአቸው መዋቾዎች አፀፋ፣ እርሻዎቻችሁ ኢንዱስትሪዎቻችሁና ንግዶቻችሁ በብዙ እጥፍ ጭማሪዎች፣ በመልካም ስጦታዎችና ገፀበረከቶች እንደሚባረኩ እርገጠኞች ሁኑ፣ አንድ መልካም ሥራ የሚሠራ አሥራ እጥፍ ዋጋ ይቀበላል፡፡ ለእነዚያ ሀብታቸውን በእርሱ መንገድ ሥራ ላይ ለሚያውሉት ሕያው ጌታ በተትረፈረፈ ሁኔታ ማረጋገጫ እንደሚሰጣቸው ምንም ጥርጥር የለውም፡፡

bahaiprayers.net
~840w BH01693
  • Fasting Prayers

ምስጋና ላንተ ይሁን፣ ጌታ አምላኬ ሆይ! ለእኔና አብረውኝ ላሉት ሁሉ፣ ከሁሉ በላይ ወደሆነው ክብርህ ሰማየ ሰማያት ለመምጠቅ የሚያስችለንንና ተጠራጣሪዎችን ወደ አንድነትህ መቅደስ ከመግባት ካገዱአቸው የጥርጣሬ ጉድፎች የሚያነፃንን እንድትልክልን፣ ጨለማውን ወደ ብርሃን በተለወጠበት፣ የሚዘወተረው መቅደስ በተገነባበት፣ ጽሁፍ መልእክት በተገለፀበትና የተዘረጋው ብራና ሽፋኑ በተነሳበት በዚህ ግልፀት እማጠንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ እኔ ያ የአፍቃሪ ደግነትህን ገመድ አጥብቄ የያዝኩ፣ በምሕረትህና በለጋስነትህ ጠርዝ ላይ የተንጠላጠልኩ ነኝ፡፡ ለእኔና ለተወዳጆቼ የዚህኛውንና የመጪውን ዓለም መልካም ነገሮች ሁሉ አዘዝልን፤ እንግዲህ ከፍጡሮችህ መካከል እጅግ በጣም ምርጥ ለሆኑት ካዘዝክላቸው ሕቡዕ ሥጦታዎች አድላቸው፤ ጌታዬ ሆይ ፣ እነዚህ ቀናት አገልጋችህ ፆም እንዲፆሙባቸው ያዘዝካቸው ናቸው፡፡ ከአንተ በስተቀር ከሌሎች ነገሮች ሁሉ ራሱን አግልሎ ለአንተ ብቻ ሲል የፆመ የተባረከ ነው፡፡ ጌታዬ ሆይ አንተን እንድንታዘዝና ሕግጋትህን እንድናከብር እርዳኝ፣ እነርሱንም እርዳቸው፣ አንተ በእውነቱ የመረጥከውን ለማድረግ ኃይል አለህና፡፡ ከአንተ ከሁሉን አዋቂው፣ ከፍጹም ጠቢቡ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ የዓለማት ሁሉ ጌታ ለሆነው የእግዚአብሔር ምስጋና ሁሉ ይሁን፤ በፆም ጊዜ የማለዳ አምላኬ ሆይ፣ ከቅርበትህ ከተማ በር አርቀህ እንዳትጥለኝና በፍጡሮችህ መካከል በፀጋህ ክስተቶች ላይ ያደረግሁአቸውን ተስፋዎች እንዳትቀጭብኝ፤ በኃያሉ ምልትህና በሰዎች መካከል በፀጋህ መገለጽ እማጠንሃለሁ፤ አምላኬ ሆይ፣ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ጠንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ሁልጊዜ ይበልጥ ወደ በርህ ደጀሰላም እንድታቀርበኝ፣ ከምህረትህ ጥላና ከቸርነትህ አጎበር እንድርቅ እንዳታደርገኝ በፍጹም ጣፋጩ ደምጽህና ፍጹም በተከበረው ቃልህ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፤ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ በመጎናፀፊያህ መዓዛ እንድትስበኝና የቃልህን ምርጥ የወይን ጠጅ እንድጠጣ እንድታደርገኝ፣ በአንፀባራቂው የግምባርህ ውበትና ከፍጹም ከፍተኛው አድማስ በሚያበራው የገጽህ ብርሃን ብሩህነት እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ ፣ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላትዬ ታየኛለህ፡፡
አምላኬ ሆይ ወደ ኋላ ሳላፈገፍግ ወይም እነዚያ በምልክቶችህ ያፌዙትና ከፊትህም የዞሩት በሚያቀርቡአቸው ሃሳቦች ሳልደናቀፍ እምነትህን እንዲገለግል በጣም እንድታነሳሳኝ፣ ልክ ፍጹም የተከበረው ብዕርህ በፍጥረትህ መንግስት ላይ የስውር ትርጉሞች ልዩ መዓዛ እያፈሰሰ በጽላቶችህ ገጾች ላይ እንደሚንቀሳቀስ ሁሉ በፊትህ ላይ በሚንቀሳቀሰው ፀጉርህ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፍጹመ ቅዱሱን ፍፁም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ በውበትህ የቀኑ ኮከብ ላይ ለማተኮር እንድታስችለኝና የልሳንህንም የወይን ጠጅ እንድታድለኝ፣ የስሞች ንጉስ በአደረግኽው በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በተመሰጡበት ስምህ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፈቃድህ ከሚጠላው ከማንኛውም ነገር እንድታርቀኝና እርሱ የአንተ ምልክቶች ጎሕ የሆነው ወደ አበራበት ደረጃ እንድታቀርበኝ፣ በመለኮታዊው ሎጥ ዛፍ መንኮሻኮሽና በስሞችህ መንግስት ውስጥ የልሳንህ ልዝብ ነፋሾች ድምጽ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውን ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፈቃድህ ከሚጠላው ከማንኛውም ነገር እንድታርቀኝና እርሱ የአንተ ምልክቶች ጎሕ የሆነው ወደ አበራበት ደረጃ እንድታቀርበኝ፣ በመለኮታዊው ሎጥ ዛፍ መንኮሻኮሽና በስሞችህ መንግስት ውስጥ የልሳንህ ልዝብ ነፋሾች ድምጽ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፍጹም ቅዱሱን፣ ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ በዕውቀትህ ማከማቻዎች ውስጥ የተደበቁትንና በጥበብህ ማስቀመጫዎች ውስጥ የተሸሸጉትን እንድትገልጥልኝ፣ በዚያ ከፈቃድህ አንደበት ከመውጣቱ ውቅያኖሶች እንዲተምሙ ነፋሶችም እንዲነፍሱ ፣ ፍሬዎችም እንዲገለጡ ዛፎችም እንዲበቅሉ፣ ያለፉት ደብዛዎች ሁሉ እንዲጠፉ ፣ ግርዶሾችም ሁሉ እንዲተረተሩ ፣ ለአንተም ያደሩት ወደማይጨቆነው የእነርሱ ጌታ ገጽታ ብርሃን እንዲለግሱ ባደረገው ፊደል እማጠንሃለሁ፣ አምላኬ ሆይ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛውም ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፤ አምላኬ ሆይ በመጽሐፍህ ውስጥ አንተ ላወረድከውና በፈቃድህም ለተከሰተው ከበቁት ጋር እንድትቆጥረኝ፣ እንቅልፍን ከሕሩያንህና ከተወዳጆችህ አይኖች ባባረረው የፍቅርህ እሳት፣ ጎህ በሚቀድበትም ሰዓት በእነርሱ አንተን ማስታወስና ማወደስ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ ፣ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን፣ ፍጹም ኃያሉን፣ ፍጹም ታላቁን፣ ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ ፣ ለታማኖችህና ለሕሩያንህ የፃፍከውን ለኔም ፍጹም በተከበረው ብዕርህ እንድትጽፍልኝ ለአንተ የቀረቡት በትዕዛዝህ ጦሮች መወጋትን እንዲቀበሉ፣ ለአንተ ያደሩትም የጠላቶችህን ሰይፎች በመነግድህ እንዲጋፈጡ ባደረጋቸው በገጽህ ብርሃን እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር ተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ወደ አንተ ለተመለሰው ለእያንዳንዱ ሰው፣ አንተ የያዝከውንም ፆም ላከበረው፣ በአንተ ፈቃድ ካልሆነ በቀር ለማናገሩትና ያላቸውንም ሁሉ በአንተ መንገድና ለአንተ ፍቅር ሲሉ ለሰውት ያዘዝከውን ካሳ እንድትጽፍለት፣ ያፍቃሪዎችህን ጥሪ፣ የእነዚያን አንተን የሚናፍቀቱትንም የኃዘን ድምጽ እነዚያ ወደ ቅርበትህ ለመግባት የታደሉት የሚያሰሙትንም ጩኽት እነዚያ ላንተ ያደሩት የሚያሰሙትንም ማቃሰት ባዳመጥህበትና በፀጋህና በቸርነትህ፣ የእነዚያን ተስፋቸውን በአንተ ላይ ያደረጉትን ሰዎች ምኞቶች በአሟላህበትና ፍላጎቶቻቸውንም በፈቀድክበት ስምህ፤ የይቅር ባይነትም ውቅያኖስ በፊትህ በተመመበትና የቸርነትህ ደመናዎች በአገልጋዮችህ ላይ በዘነቡበት ስምህ እማጠንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ፣ እነዚያ ህግጋትህን አጥብቀው የያዙትና በመጽሐፍህ ውስጥ የደነገግህላቸውን ያከበሩት የፈፀሙትን በደል ትሰርዝላቸው ዘንድ በአንተው በራስህ በምልክቶችህ በግልጽ መታወቂያዎችህ በሚያበራው የውበትህ የቀኑ ኮከብ ብርሃንና በቅንጫፎችህ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፤

bahaiprayers.net
~839w BH00868WIT
  • Fasting

ምስጋና ላንተ ይሁን፣ ጌታ አምላኬ ሆይ! ለእኔና አብረውኝ ላሉት ሁሉ፣ ከሁሉ በላይ ወደሆነው ክብርህ ሰማየ ሰማያት ለመምጠቅ የሚያስችለንንና ተጠራጣሪዎችን ወደ አንድነትህ መቅደስ ከመግባት ካገዱአቸው የጥርጣሬ ጉድፎች የሚያነፃንን እንድትልክልን፣ ጨለማውን ወደ ብርሃን በተለወጠበት፣ የሚዘወተረው መቅደስ በተገነባበት፣ ጽሁፍ መልእክት በተገለፀበትና የተዘረጋው ብራና ሽፋኑ በተነሳበት በዚህ ግልፀት እማጠንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ እኔ ያ የአፍቃሪ ደግነትህን ገመድ አጥብቄ የያዝኩ፣ በምሕረትህና በለጋስነትህ ጠርዝ ላይ የተንጠላጠልኩ ነኝ፡፡ ለእኔና ለተወዳጆቼ የዚህኛውንና የመጪውን ዓለም መልካም ነገሮች ሁሉ አዘዝልን፤ እንግዲህ ከፍጡሮችህ መካከል እጅግ በጣም ምርጥ ለሆኑት ካዘዝክላቸው ሕቡዕ ሥጦታዎች አድላቸው፤ ጌታዬ ሆይ ፣ እነዚህ ቀናት አገልጋችህ ፆም እንዲፆሙባቸው ያዘዝካቸው ናቸው፡፡ ከአንተ በስተቀር ከሌሎች ነገሮች ሁሉ ራሱን አግልሎ ለአንተ ብቻ ሲል የፆመ የተባረከ ነው፡፡ ጌታዬ ሆይ አንተን እንድንታዘዝና ሕግጋትህን እንድናከብር እርዳኝ፣ እነርሱንም እርዳቸው፣ አንተ በእውነቱ የመረጥከውን ለማድረግ ኃይል አለህና፡፡ ከአንተ ከሁሉን አዋቂው፣ ከፍጹም ጠቢቡ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ የዓለማት ሁሉ ጌታ ለሆነው የእግዚአብሔር ምስጋና ሁሉ ይሁን፤ በፆም ጊዜ የማለዳ አምላኬ ሆይ፣ ከቅርበትህ ከተማ በር አርቀህ እንዳትጥለኝና በፍጡሮችህ መካከል በፀጋህ ክስተቶች ላይ ያደረግሁአቸውን ተስፋዎች እንዳትቀጭብኝ፤ በኃያሉ ምልትህና በሰዎች መካከል በፀጋህ መገለጽ እማጠንሃለሁ፤ አምላኬ ሆይ፣ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ጠንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ሁልጊዜ ይበልጥ ወደ በርህ ደጀሰላም እንድታቀርበኝ፣ ከምህረትህ ጥላና ከቸርነትህ አጎበር እንድርቅ እንዳታደርገኝ በፍጹም ጣፋጩ ደምጽህና ፍጹም በተከበረው ቃልህ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፤ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ በመጎናፀፊያህ መዓዛ እንድትስበኝና የቃልህን ምርጥ የወይን ጠጅ እንድጠጣ እንድታደርገኝ፣ በአንፀባራቂው የግምባርህ ውበትና ከፍጹም ከፍተኛው አድማስ በሚያበራው የገጽህ ብርሃን ብሩህነት እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ ፣ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላትዬ ታየኛለህ፡፡
አምላኬ ሆይ ወደ ኋላ ሳላፈገፍግ ወይም እነዚያ በምልክቶችህ ያፌዙትና ከፊትህም የዞሩት በሚያቀርቡአቸው ሃሳቦች ሳልደናቀፍ እምነትህን እንዲገለግል በጣም እንድታነሳሳኝ፣ ልክ ፍጹም የተከበረው ብዕርህ በፍጥረትህ መንግስት ላይ የስውር ትርጉሞች ልዩ መዓዛ እያፈሰሰ በጽላቶችህ ገጾች ላይ እንደሚንቀሳቀስ ሁሉ በፊትህ ላይ በሚንቀሳቀሰው ፀጉርህ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፍጹመ ቅዱሱን ፍፁም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ በውበትህ የቀኑ ኮከብ ላይ ለማተኮር እንድታስችለኝና የልሳንህንም የወይን ጠጅ እንድታድለኝ፣ የስሞች ንጉስ በአደረግኽው በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በተመሰጡበት ስምህ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፈቃድህ ከሚጠላው ከማንኛውም ነገር እንድታርቀኝና እርሱ የአንተ ምልክቶች ጎሕ የሆነው ወደ አበራበት ደረጃ እንድታቀርበኝ፣ በመለኮታዊው ሎጥ ዛፍ መንኮሻኮሽና በስሞችህ መንግስት ውስጥ የልሳንህ ልዝብ ነፋሾች ድምጽ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውን ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፈቃድህ ከሚጠላው ከማንኛውም ነገር እንድታርቀኝና እርሱ የአንተ ምልክቶች ጎሕ የሆነው ወደ አበራበት ደረጃ እንድታቀርበኝ፣ በመለኮታዊው ሎጥ ዛፍ መንኮሻኮሽና በስሞችህ መንግስት ውስጥ የልሳንህ ልዝብ ነፋሾች ድምጽ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፍጹም ቅዱሱን፣ ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ በዕውቀትህ ማከማቻዎች ውስጥ የተደበቁትንና በጥበብህ ማስቀመጫዎች ውስጥ የተሸሸጉትን እንድትገልጥልኝ፣ በዚያ ከፈቃድህ አንደበት ከመውጣቱ ውቅያኖሶች እንዲተምሙ ነፋሶችም እንዲነፍሱ ፣ ፍሬዎችም እንዲገለጡ ዛፎችም እንዲበቅሉ፣ ያለፉት ደብዛዎች ሁሉ እንዲጠፉ ፣ ግርዶሾችም ሁሉ እንዲተረተሩ ፣ ለአንተም ያደሩት ወደማይጨቆነው የእነርሱ ጌታ ገጽታ ብርሃን እንዲለግሱ ባደረገው ፊደል እማጠንሃለሁ፣ አምላኬ ሆይ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛውም ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፤ አምላኬ ሆይ በመጽሐፍህ ውስጥ አንተ ላወረድከውና በፈቃድህም ለተከሰተው ከበቁት ጋር እንድትቆጥረኝ፣ እንቅልፍን ከሕሩያንህና ከተወዳጆችህ አይኖች ባባረረው የፍቅርህ እሳት፣ ጎህ በሚቀድበትም ሰዓት በእነርሱ አንተን ማስታወስና ማወደስ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ ፣ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን፣ ፍጹም ኃያሉን፣ ፍጹም ታላቁን፣ ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ ፣ ለታማኖችህና ለሕሩያንህ የፃፍከውን ለኔም ፍጹም በተከበረው ብዕርህ እንድትጽፍልኝ ለአንተ የቀረቡት በትዕዛዝህ ጦሮች መወጋትን እንዲቀበሉ፣ ለአንተ ያደሩትም የጠላቶችህን ሰይፎች በመነግድህ እንዲጋፈጡ ባደረጋቸው በገጽህ ብርሃን እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር ተመላውን ስምህን እንደያዝኩ፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ወደ አንተ ለተመለሰው ለእያንዳንዱ ሰው፣ አንተ የያዝከውንም ፆም ላከበረው፣ በአንተ ፈቃድ ካልሆነ በቀር ለማናገሩትና ያላቸውንም ሁሉ በአንተ መንገድና ለአንተ ፍቅር ሲሉ ለሰውት ያዘዝከውን ካሳ እንድትጽፍለት፣ ያፍቃሪዎችህን ጥሪ፣ የእነዚያን አንተን የሚናፍቀቱትንም የኃዘን ድምጽ እነዚያ ወደ ቅርበትህ ለመግባት የታደሉት የሚያሰሙትንም ጩኽት እነዚያ ላንተ ያደሩት የሚያሰሙትንም ማቃሰት ባዳመጥህበትና በፀጋህና በቸርነትህ፣ የእነዚያን ተስፋቸውን በአንተ ላይ ያደረጉትን ሰዎች ምኞቶች በአሟላህበትና ፍላጎቶቻቸውንም በፈቀድክበት ስምህ፤ የይቅር ባይነትም ውቅያኖስ በፊትህ በተመመበትና የቸርነትህ ደመናዎች በአገልጋዮችህ ላይ በዘነቡበት ስምህ እማጠንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ፣ እነዚያ ህግጋትህን አጥብቀው የያዙትና በመጽሐፍህ ውስጥ የደነገግህላቸውን ያከበሩት የፈፀሙትን በደል ትሰርዝላቸው ዘንድ በአንተው በራስህ በምልክቶችህ በግልጽ መታወቂያዎችህ በሚያበራው የውበትህ የቀኑ ኮከብ ብርሃንና በቅንጫፎችህ እማጠንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ ፍጹም ቅዱሱን ፍጹም አንፀባራቂውን ፍጹም ኃያሉን ፍጹም ታላቁን ፍጹም የተከበረውንና ፍጹም ክብር የተመላውን ስምህን እንደያዝኩ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያሉት ሁሉ በተንጠላጠሉበት የካባህ ዘርፍ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፤

bahaiprayers.net
Also in: af eu bs bg da nl en eo et fr de el ht hu it lv mh no pl pt ro es sv tl
~66w AB00362LOV
አቤቱ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ! የእውነተኛ አፍቃሪዎችህን ግንባር አብራላቸው፣ የተረጋገጠ ድል በሚያስገኙ መልአካዊ ሠራዊትም ደግፋቸው የእምነትህን ደህንነት በመጠበቅ፣ እምነታቸውን በአንተ ትዝታ ላይ በማድረግ ልቦቻቸውን ለአንተ ፍቅር በመስጠት፣ ውበትህን በማወደስና አንተን የሚያስደስቱበትን መንገድ በመፈለግ ለሀብታቸው ሳይሳሱ የለገስካቸውን ሁሉ በጎዳናህ በማዋላቸው፣ እግሮቻቸውን በቀጥተኛው መንገድህ ላይ አበርታላቸው ከጥንታዊው ቸርነትህም የቡራኬዎችህን በሮች ክፈትላቸው፤ ጌታዬ ሆይ! የተትረፈረፈ ድርሻ፣ የተመደበ ካሣና የተረጋገጠ ሽልማት እዘዝላቸው፤ በእውነቱ አንተ ደጋፊው ረዳቱ ለጋሱ በረከት የተመላው፣ዘለዓለም ሰጪው ነህና፤
bahaiprayers.net
Also in: bn nl en hu is id mn pl pt ro ru es sv ta
~367w AB07850
  • Infants ጌታ አምላኬ ሆይ፡ ምስጋና ለአንተ ይሁን ይህ ህፃን በፀጋህ የፍቅራዊ ምሕረትህንና ርኅራኁ የተመላበት የአምላካዊ ጥበቃህን ጡት እንዲጠባ የመንግስተ ሰማያዊ ዛፎችህንም ፍሬዎች እንዲመገብ ፈቃድህ ይሁን፡፡ አንተ ራስህ በላቀው ፈቃድህና ሥልጣንህ ኃይል ስለፈጠርከውና ወደ መኖር ስለጠራኽው ለአንተ እንጂ ለሌላ ለማንም እንክብካቤ እንዲተው አታድርገው ከአንተ ከፍፁም ኃያሉ ከሁሉን አዋቂው በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ አቤቱ አንተ ከሁሉም በላይ ተወዳጄ ሆይ፤ የተወደስክ ነህ ከሁሉ የላቀ በረከትህን ጣፋጭ ሽታና የቅዱስ ስጦታዎችህን መዓዛዎች በላዩ አርብብበት፡፡ ከዚያም አቤቱ አንተ ስሞችና የባህርያት መንግስትን በመዳፈህ ውስጥ ይዘህ ያለኽው ሆይ ከሁሉም በላይ በተከበረው ስምህ ጥላ ሥር መጠለያ ለመፈለግ አስችለው፤ በእውነቱ አንተ የፈቀድከውን ለማድረግ የማይሳንህ ነህ፤ በእርግጥም አንተ ኃያሉ የተከበረው ዘለዓለም ይቅር ባዩ ፀጋ የተመላው ለጋሱ መሐሪው ነህና፤ ጌታ አምላኬ ሆይ ይህ አንተ በማይሻረው ትዕዛዝህ መልእክቶችና በፈቃድህ መፃሕፍት ውስጥ የተከበረ ደረጃ እንዲኖራቸው ከፈቀድህላቸው አገልጋዮችህ መካከል ከአንዱ አብራክ የተገኘ ልጅ ነው፡፡ ይህ ልጅ በአገልጋዮችህ መካከል በሳል ነፍስ እንዲሆን ፈቃድህ ይሆን ዘንድ፣ እያንዳንዱን ሰው ወደ ፍላጎቱ ዓላማ ለመድረስ በአስቻልክበት ስምህ እማፀንሃለሁ፣ በስምህ ኃይል አማካይነት እንዲያበራ አድርገው፣የአንተን ምስጋና ለመናገር ፊቱን ወደ አንተ ለመመለስና ወደ አንተ ለመቅረብ አስችለው በእውነቱ ከእምቅድመ ዓለም ጀምሮ እንደፈቃድህ ለማድረግ ኃይል የነበረህ፣እስከ ዘለዓለምም የፈቀድኽውን ለማድረግ የማይሳንህ ሆነህ የምትኖረው አንተ ነህ፤ ከአንተ ከተከበረው ግርማ ሞገስ ከተመላው ከድል አድራጊው ከኃያሉ፣ ከሁሉን አስገዳጁ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ጌታዬ ሆይ ጌታዬ ሆይ በለጋነት ዕድሜ ያለሁ ሕፃን ነኝ፡፡ ከምሕረትህ ጡት ወተት መግበኝ፣ በፍቅርህ እቅፍ ውስጥ አሰልጥነኝ፣ በአንተ መርሖ ትምህርት ቤት አስተምረኝ፣ በበረከትህ ጥላ ሥር አጎልምሰኝ፤ ከጨለማ አውጣኝ ደማቅ ብርሃን አድርገኝ ከደስታ ማጣት አድነኝ፣የጽጌረዳ አትክልት ሥፍራ አበባ አድርገኝ የደጀሰላምህ አገልጋይ እንድሆን አድርገኝ የፃድቃንንም ዝንባሌና ጠባይ አጎናጽፈኝ ፣ለሰው ዘር ዓለም የበረከት መንስኤ አድርገኝ፣ በራሴም ላይ የዘለዓለም ህይወት አክሊል ድፋልኝ! በእውነቱ አንተ ኃይል የተመላው ኃያሉ፣ ሁሉን የሚያው ሰሚው ነህና፤ አምላኬ ሆይ ምራኝ፣ ጠብቀኝ ብሩህ መብራትና አንፀባራቂ ኮከብ አድርገኝ፣ አንተ ኃያሉና ኃይል የተመላው ነህና፤ አምላክ ሆይ እነዚህን ህፃናት አስተምራቸው እነዚህ ህፃናት የአትክልት ሥፍራህ ተክሎች የመስክህ አበባዎች አትክልት ቦታህ ፅጌረዳዎች ናቸው፡፡ ዝናብህ እንዲዘንብላቸው የአውነት ፀሐይ ከፍቅርህ ጋር እንዲበራላቸው አድርግ፣ ይሠለጥኑ ያድጉና ይዳብሩ፣ በከፍተኛ ውበትም ይታዩ ዘንድ፣ የአንተ ልዝብ ነፋስ እንዲያድሳቸው ፈቃድህ ይሁን አንተ ሰጪው ነህ፡፡ አንተ ሩኅሩኁ ነህ፡፡ አምላክ ሆይ ይህን ጨቅላ ህፃን በፍቅርህ ጉያ ተንከባከበው ከመለኮታዊ ጠባቂነትህም ጡት ወተት ለግሰው፡፡ ይህን ለጋ ቡቃያ በፍቅርህ የጽጌረዳ አትክልት ሥፍራ ውስጥ ኮትኩተህ አሳድገው፤ ከፀጋህም በሚወርደው ዝናብ እንዲያድግ እርዳው፡፡ የመንግስተ ሰማይ ልጅ አድርገው ወደ መንግስተ ሰማያዊው ዓለምህም ምራው ፡፡ አንተ ኃይል የተመላህና ደግ ነህ፣ አንተ ሰጪው ቸሩ፣የተትረፈረፈ በረከት ባለቤት ነህና፤
bahaiprayers.net
~857w BH03181
እርሱ ለጋሱ ፡ ጸጋ የተመላው ነው፤
በእውነቱ እርሱ አንዱ፡ አንድዬው የማይታው የተከበረው መሆኑን በገዛ ራሱ ሕያውነት ለመሠከረው፣ለጥንታዊው ፣ ለዘላለም ነዋሪው ለማይለወጠው፣ ለዘላለማዊው አምላክ ምስጋና ይሁን! በእውነቱ የእርሱን አንድነት በማረጋገጥ የእርሱን አንድዬነት በመቀበል ከእርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ እንመሰክራለን፡፡ እርሱ ከእርሱ ከራሱ በስተቀር ከሌላ ከማንም ገለፃ ነፃ ሆኖ፣ ወደ አቅራቢያቸው ለመድረስ በማይቻሉ ከፍታዎች፣ በላቀ ደረጃው የላቁ ከፍታዎች ላይ ለዘለዓለም ኖሮአል፡፡ እርሱ ፀጋንና በጎ ፈቃድን ለሰዎች ለመግለፅ፣ ያለምንም ሥርዓት ለማስያዝ ስለፈለገ፣ ትዕዛዛትን ገለፀ፣ ሕግጋትንም ደነገገ፣ በእነዚህም ሕግጋት መካከል የጋብቻን ሕግ መሠረተ፣ የደህንነትና የዳንም ምሽግ አደረገው፣ ከቅድስና መንግሥተ ሰማይም በተላከው በእርሱ ከሁሉም በላይ ቅዱስ በሆነው መጽሐፍ ውስጥ እንድናከብረው አዘዘን፡፡ የእርሱ ክብር ታላቅ ነው! እንዲህ ይላል፣ ሰዎች ሆይ፣ በአገልጋዮቼ መካከል እኔን የሚያስታውስ ከእናንተ ይገኝ ዘንድ ተጋቡ፣ ይህ ለእናንተ ከትዕዛዞቼ መካከል አንዱ ነው፤ ለእናንተ ለራሳችሁ እንዲራዳችሁ ታዘዙት፡፡ አምላኬ ሆይ፣ ክብር ለአንተ ይሁን! በእውነቱ ይህ አገልጋይህና ይህች አገልጋይህ በምሕረትህ ጥላ ሥር ተሰባስበው÷ በአንተ ደግነትና ቸርነት በጋብቻ ተጣምረዋል፡፡ ጌታ ሆይ ! በዚህ ዓለምህና በመንግስትህ ውስጥ እርጃቸው በቸርነትህና በፀጋህ እያንዳንዱን መልካም ነገር አድላቸው፡፡ ጌታ ሆይ! ለአንተ በአገልጋይነታቸው ተግባር ላይ አበርታቸው፤ ለአንተ እንዲያገለግሉ፤ በዓለምህም የስምህ ምልክቶች እንዲሆኑ አድርጋቸው፤ በዚህ ዓለምና በሚቀጥለውም ዓለም በማያልቁ ችሮታዎችህ ጠብቃቸው፡፡ ጌታ ሆይ! የመሀሪነትህን መንግስት እየተማፀኑ፣ የአንድነትህንም ዓለም እርዳታ እየጠየቁ ናቸው፡፡ በእውነቱ የአንተን ትዕዛዝ በማክበር ተጋብተዋል፡፡ እስከ መጨረሻው ጊዜ ድረስ የስምምነትና የአንድነት ምልክቶች እንዲሆኑ አድርጋቸው፣ በእውነቱ አንተ ምንም የማይሳነው፣ በሁሉ ሥፍራ የሚገኘውና ፍጹም ኃያሉ ነህና፤ የፈውስ አምላኬ ሆይ፣ ስምህ መፈወሻ ነው፣ አንተንም ማስታወስ መድኃኒቴ ነው፡፡ ወደ አንተ መቅረብ ተስፋዬ ነው፣ ለአንተም ያለኝ ፍቅር ባልደረባዬ ነው፡፡ የአንተ ምሕረት በዚህና በሚቀጥለው ዓለም መፈወሻዬና እርዳታዬ ነው፡፡ በእውነቱ አንተ ፍጹም ለጋሱ፣ ሁሉን አዋቂው ፍጹም ጠቢቡ ነህና፤ በፈዋሹ በአርኪው በረዳቴ በእግዚአብሔር ስም! አምላክ ሆይ ምስጋና ለአንተ ይሁን! አምላኬና ተወዳጄ ሆይ! አቤቱ አንተ የመጨረሻ ዕድል መንግስትና ተፈፃሚ የማድረግ ሥልጣን በመዳፍህ ውስጥ ያለው ሆይ፤ በዚህ ሕመመተኛ ላይ ከእያንዳንዱ በሽታ ድክመትና ፈተና የሚያነፃውን ከምህረትህ ደመናዎች እንድታዘንብበት በመፈወሻህም ውቅያኖስ ውስጥ እንድታሰጥመው፤ ምሕረትህ ሁሉን ነገር በቀደመበት ስምህ፣ ከገጽታህ አድማስ ባበራውና ፀጋህ በእነዚያ በምድርና በሰማይ በሚገኙት ሁሉ ላይ ፍፁም በሆነበት በህቡዕ ስምህ ውበት ፀሐይ እለምንሃለሁ፡፡ በእውነቱ፣ አንተ የፈቀደውን ሁሉ አድራጊው ነህና በእርግጥም አንተ ይቅር ባዩና አዛኜ ነህና፡፡ ጌታ አምላኬ ሆይ፣ ክብር ለአንተ ይሁን ይህቺን ለመጠጊያ ወደ አንተ የሸሸችውን የእርሱን አንተ ራስህን በእርሱ ላይ የከሰትከውን ተገን የፈለገችውን መላ እምነተንና ተስፋዋንም በአንተ ላይ የጣለችውን ሴት አገልጋይ እንድትጠብቅ እርሱ የአንተ ውበት የሆነው በእምነትህ ዙፋን ላይ በተሰየበት ስምህ አንተም ሁሉንም ነገሮች በምትለውጥበት ሁሉንም ነገሮች አንድ ላይ በምትሰበስብበት፣ ሁሉንም ነገሮች ስለሥራቸው ልትጠይቃቸው በምትጠራበት፣ ለሁሉም ነገሮች ወሮቻቸውን በምትሰጥበት ሁሉንም ነገሮች ጠብቀህ በምታቆይበት ሁሉንም ነገሮች በሕይወት በምታኖርበት ስምህ እለምንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ እርሷ ታማ በመፈወሻህ ዛፍ ጥላ ሥር ገብታለች፡፡ ተሰቃይታ ወደ ጥበቃህ ከተማ ሸሽታለች፤ በሽተኛ ሆና የችሮታህን ምንጭ መነሻ ፈልጋለች፤ ክፉኛ ተበሳጭታ ወደ ማረጋጋትህ ምንጭ ለመድረስ በፍጥነት ገስግሳለች፤ በኃጢአት ሸክም ተጨንቃ ፊቷን ወደ ይቅር ባይነትህ መንበር መልሳለች፡፡ አምላኬና ተወዳጄ ሆይ በሥልጣንህና በፍቅራዊ ደግነትህ፣ በአዳኝ ቅባትህና በመፈወሻህ ልብስ አልብሳት፣ ከምሕረትህና ከችሮታህ ጽዋ እስክትረካ እንድትጠጣ አድርጋት፡፡ በተጨማሪም፣ ከእያንዳንዱ መከራና ሕመም፣ ከሁሉም ስቃይና በሽታ ለአንተ ከሚያስጠይፈቅ ከማንኛውም ነገር ጠብቃት፡፡ አንተ በእውነቱ ከአንተ ከራስህ በስተቀር ከሌላው ሁሉ በላይ በጣም የላቅህና የተከበርክ ነህ፡፡ በእውነቱ አንተ ፈዋሹ ፍጹም አርኪው ጠብቆ አኑዋሪው፣ ዘላለም ይቅር ባዩ፤ ከሁሉ በላይ መሐሪው ነህና፡፡ አምላኬ ሆይ አንተ በስሞቹ ሕመምተኞች የሚፈወሱት በሽተኞችም የሚድኑት፣ የተጠቀሙትም የሚረኩት ክፉኛ የተበሳጩትም የሚረጋጉት መንገድ የሳቱትም የሚመሩት የተዋረዱትም የሚከበሩት ድሆችም የሚበለጽጉት አላዋቂዎችም ዕውቀት የሚያገኙት፣ የተከዙትም የሚደሰቱት ኃዘንተኞችም የሚጽናኑት፣የቀዘቀዙትም የሚሞቁት የተረገጡትም ከፍ የሚደረጉት ነህ፡፡ አምላኬ ሆይ በስምህ አማካይነት የተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ ተቀሰቀሱ፣ሰማያትም ተዘረጉ ምድርም ተመሠረተች፤ ደመናዎቹም እንዲንሳፈፉና በምድር ላይ እንዲያዘንቡ ተደረጉ፡፡ ይህም በእውነቱ ለፍሮችህ ሁሉ የአንተ ፀጋ ምልክት ነው፡፡
ስለዚህ በዚህ ሌሊት በዚህ አንተ በፍጥረትህ መንግስት ከአንተ ፍፁም ክብር የተመላ ህልውና ጋር በአዛመድኽው ሕፃን ላይ ከምሕረትህ ደመናዎች የመፈወሻህን ዝናቦች እንድታዘንብበት አንተ አምላክነትህን በከሰትህበት እምነትህንም ከፍጥረት ሁሉ በላይ ከፍ በአደረግህበት ስምህ፣ የአንተ ከሁሉ የላቁ ስያሜዎችና ከሁሉም በላይ የተከበሩ ባህርያት የአንተ ከሁሉ የላቀውና ከሁሉም በላይ የተከበረው ሕያውነት በሚወደስባቸው ባህርያት ሁሉ እማፀንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ በአንተ ፀጋ በደህንነትና በጤና ልብስ አልብሰው አቤቱ አንተ ተወዳጄ ሆይ ከእያንዳንዱም ስቃይና ሕመም ለአንተም ከሚያስጠላው ከማንኛውም ነገር ጠብቀው በእውነቱ የአንተ ኃያልነት ለሁሉም ነገሮች ብቁ ነው፡፡ በእውነቱ አንተ ከሁሉም በላይ ኃይል የተመላው በገዛ ራሱም ነዋው ነህ፡፡ ከዚህም በላይ አምላኬ ሆይ የዚህንና የሚቀጥለውን ዓለም መልካም ነገሮች የቀድሞዎችንም የኋለኞችንም ትውልዶች መልካም ነገሮች ሁሉ ላክለት፡፡ በእውነቱ የአንተ ኃይልነትና የአንተ ጥበብ ለዚህ ሁሉ ብቁ ናቸውና፡፡ ጌታ አምላኬ ሆይ፤ ክብር ለአንተ ይሁን ተማጽኜሃለሁ እርሱን አንተን በጽናት በመያዝ ወደ አንተ የተመለሰውን በምሕረትህም ላይ የተንጠላጠለውን የፍቅራዊ መለኮታዊ ጥበቃህንም ዘርፍ አጥብቆ የያዘውን ከማንኛውም አደጋ እንድትጠብቀው በእርሱ አማካይነት የአንተን መርሐ ግርማዎች ከፍ በአደረግህበት፣ የፍቅራዊ ደግነትህንም ብርሃን በአበራህበት፣ የጌታነትህንም ሥልጣን በገለጽህበት፣ የስሞችህም ፋኖስ በባህርያትህ መቅረዝ ላይ በተከሰተበት እርሱም የአንድነትህ መቅደስና የመላቀቅ ክስተት የሆነው በአበራበት፣ የአንተ መርሐ ጎዳናዎችም በታወቁበት የበጎ ፈቃድህም መንገዶች በተቀየሱበት የስህተት መሠረቶች እንዲንቀጠቀጡ የክፋት ምልክቶችም እንዲጠፉ በተደረጉበት የጥበብ ምንጮችም በፈለቁበት መንግስተ ሰማያውያም ገበታ ከላይ በተላከበት፣ አገልጋችህንም ጠብቀህ በአኖርክበትና ፈውስህንም በለገስክበት ፣ ለአገልጋችህ ርህራሄ የተመላበት ምሕረትህን በአሳየህበትና በፍጡራንም መካከል ይቅር ባይነትህን በገለፅክበት ስምህ እማፀንሃለሁ፡፡ እንግዲህ ፈውስህን ላክለት፣ የተሟላም አድርገው በአንተ የተለገሰ ጽናት በከፍተኛነትህም የተበረከተ መረጋጋት አጎናጽፈው፣ በእውነቱ አንተ ፈዋሹ አኑዋሪው ረዳቱ ፍጹም ኃያሉ ኃይል የተሞላው፣ ንዑዱ ሁሉን አዋቂው ነህና፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ሆይ! በበረከትህ ውሀዎች አማካይነት ከእያንዳንዱ ስቃይና የጤና መቃወስ፣ ከማናቸውም ድክመትና አቅመ ቢስነት ሁሉ እንድታነፃኝ፣ በመፈወሻህ ውቅያኖስም በፀጋህ የቀኑ ኮከብ ብርሃን ውበትም÷ አገልጋዮችህን በአስገበርክበት ስምህም÷ ከሁሉ በላይ በተከበረው ቃልህ ሁሉን የሚናኝ ኃይልም÷ ከሁሉ በላይ ግርማ በተመላው ብዕርህ ሁሉን ቻይነትም፣ በሰማይና በምድር ከሚገኙት ሁሉ መፈጠር በቀደመው ምሕረትህም እለምንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ ተማፀኝህ በበረከትህ በር ላይ ሲጠባበቅ፣ እርሱ ተስፋውን በአንተ ላይ ያደረገውም በቸርነትህ ገመድ ላይ ተንጠላጥሎ ታየዋለህ፤ እር ከፀጋህ ውቅያኖስና ከፍቅራዊ ደግነትህ የቀኑ ኮከብ የሚፈልጋቸውን ነገሮች እንዳትነፍገው እማፀንሃለሁ፡፡ አንተ የሚያስደስትህን ለማድረግ ኃይል አለህ፡፡ ከአንተ ከምንጊዜም ይቅር ባዩ ከፍፁም ቸሩ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡
bahaiprayers.net
~73w AB00001ABI
  • Marriage

የእግዚአብሔር ወዳጆች ሁሉ፣ የሚሰጡት ምንም ያህል ትንሽ ቢሆንም እንኳ፣ የሚችሉትን ያህል ማዋጣት አለባቸው፣ እግዚአብሔር ማንኛዋንም ነፍስ ከአቅሟ በላይ አይፈልግባትም፡፡ እንዲህ ያለው መዋጮ ከሁሉም ማዕከሎችና ከሁሉም ምዕመናን መምጣት አለበት፤ የእግዚአብሔር ወዳጆች ሆይ ለእነዚህ ለምታዋጡአቸው መዋቾዎች አፀፋ፣ እርሻዎቻችሁ ኢንዱስትሪዎቻችሁና ንግዶቻችሁ በብዙ እጥፍ ጭማሪዎች፣ በመልካም ስጦታዎችና ገፀበረከቶች እንደሚባረኩ እርገጠኞች ሁኑ፣ አንድ መልካም ሥራ የሚሠራ አሥራ እጥፍ ዋጋ ይቀበላል፡፡ ለእነዚያ ሀብታቸውን በእርሱ መንገድ ሥራ ላይ ለሚያውሉት ሕያው ጌታ በተትረፈረፈ ሁኔታ ማረጋገጫ እንደሚሰጣቸው ምንም ጥርጥር የለውም፡፡

bahaiprayers.net
Also in: da en is it kl kn mg pt sv
~162w BH09401
በፆም ወይም በሌሎች የማለዳ ጊዜያት የሚደረግ አምላኬ ጌታዬ ሆይ! እኔ አገልጋይህ የአገልጋይህም ልጅ ነኝ፡፡ የአንድነትህ የቀኑ ኮከብ ከፈቃድህ ጎሕ በበራበትና በትዕዛዝህ መፃሕፍት ውስጥ በተደነገገው መሠረት ጮራውን በመላው ዓለም ላይ በፈነጠቀበት በዚህ ማለዳ ከመደቤ ነቅቻለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ ወደ ዕውቀትህ ብርሃን ውበት ለመንቃት በመቻላችን ለአንተ ምስጋና ይድረስህ፡፡ ጌታዬ ሆይ አንተን በስተቀር ሌላውን ሁሉ ለመተው የሚያስችለንንና ከአንተ በስተቀር ከማንኛውም ቁራኛነት የሚያነፃንን ላክልን፡፡ በተጨማሪም ለእኔ ለእኔ ውድ ለሆኑትና ለዘመዶቼ፤ ለወንዱም ለሴቱም የዚህኛውንና የመጪውን ዓለም መልካም ነገር ሁሉ እዘዝልን፡፡ አቤቱ አንተ የመላው ፍጥረት ተወዳጅና የጠቅላላው ሁለንተን ዓለም ምኞት የሆንክ ሆይ፣ የእርኩሱ አንሾኳሻኪ መገለጫዎች ከአደረግሃቸው ከእነዚያ በሰዎች ልቦናዎች ከሚያንሾኳሹኩት፤ በማይቋረጠው ጠባቂነትህ ጠብቀን፡፡ አንተ የፈቀድከውን ለማድረግ የማይሳንህ ነህና፡፡ በእውነቱ አንተ ፍጹም ኃያሉ፤ በአደጋ ጊዜ ረዳቱ በገዛ ራሱም ነዋሪው ነህና ፡፡
ጌታ አምላኬ ሆይ ፤ እርሱን ከሁሉም በላቁት ስያሜዎችህ ላይ የሰየምከውን በእርሱም ፃድቃንን ከኃጢአን የለየህበትን ባርከው፣ እኛም አንተ የምትፈቅደውንና የምትወደውን እንድንሠራ በፀጋህ እርዳን፣ በተጨማሪም አምላኬ ሆይ የአንተ ቃላትና ፊደላት የሆኑትን ፊታቸውን ወደአንተ ያቀኑትን ወደአንተም ገጽታ የዞሩትን ጥሪህንም ያዳመጡትን ሁሉ ባርካቸው፤ በእውነቱ አንተ የሰዎች ሁሉ ጌታና ንጉሥ በሁሉም ነገሮች ላይየበላይ ነህ፡፡
bahaiprayers.net
~815w BH10581
  • Thanksgiving

አምላኬ ሆይ፣ የክብርና የግርማ፣ የታላቅነትና የክቡርነት፣ የሉዓላዊነትና የገዢነት፣ የልዕልናና የፀጋ የመከበርና የስልጣን ሁሉ ምንጭ ለሆንከው ለአንተ ብቻ ምስጋና ሁሉ ይድረስህ፡፡ አንተ የምትፈቅደውን ሁሉ ወደ እጅግ በጣም ታላቁ ውቅያኖስ እንዲቀርብ ታደርገዋለህ፤ የመትወደውንም ሁሉ ዘለዓለማዊ ስምህን የማወቅን ክብር ታጎናጽፈዋለህ፡፡ በሰማያትና በምድር ካሉት ሁሉ የከፍተኛ ፈቃድህን ፍፃሜ ሊያስቀር የሚችል ከቶ አይገኝም፡፡ ከእምቅድመ ዓለም ጀምረህ ፍጥረትን ሁሉ ገዝተሃል፣ እስከ ዘለዓለምም በፍጡራን ሁሉ ላይ ገዥነትህ ከቶ አያቋርጥም፡፡ ከአንተ ከፍጹም ኃያሉ፣ ከሁሉም በላይ ከተከበረው፣ ፍጹም ኃይል ከተመላው ከፍጹም ጠቢቡ በስተቀርሌላ አምላክ የለም፡፡ ጌታ አምላኬ ሆይ፣ አገልጋዮችህ አንተን ለማየት ይችሉ ዘንድ ፎቶቻቸውን አብራላቸው፣ ወደ መንግስተ ሰማያዊ ችሮታዎችህ መንበር እንዲዞሩ፣ እርሱን የአንተ የራስህ ክስተትና የህላዌህ ጎሕ የሆነውን እንዲያውቁ ልቦቻቸውን አንፃ፡፡ በእውነቱ አንተ የዓለማት ሁሉ ጌታ ነህና ከአንተ ጨቋኝ ከሌለበትና ሁሉን ድል ከሚነሣው በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ የተመሰገንክና የተወደስክ ነህ፣ ጌታ አምላኬ ሆይ! ምንም ያህል ጥበቡ የጠለቀ አንደበት ስምህን በተገቢ ሁኔታ ለማወደስ እንደማይችል፣ የሰው ልብ ወፍም፣ ምንም ያህል ታላቅ ናፍቆትና ፍላጎት ቢኖረውም፣ ወደ ግርማህና ወደ ዕውቀትህ ሰማይ ሊያደርግ እንደማይችል እያወቅሁ፣ እንዴት ስምህን ላነሳ እችላለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ! ሁሉን የሚያስተውል ብዬ ብገልጽህ፣ እነዚያ ፍጹም ከፍተኞቹ የማስተዋል ክስተቶች በአንተ ትዕዛዝ መፈጠራቸውን እንድቀበል እገደዳለሁ፡፡ ፍጹም ጠቢቡ ብዬ ባወድስህም፣ እንደገና የጥበብ ምንጮች የሆኑት ራሳቸው በአንተ ፈቃድ መፍለቃቸውን እንዳውቅ እገደዳለሁ፡፡ ተወዳደሪ የሌለው ብዬ ብገልጽህም ፣ እነዚያ የአንድነት ውስጣዊ ህልውና የሆኑት በአንተ ወደዚህ የተላኩና የአንተ የእጅ ጥበብ ማረጋገጫዎች መሆናቸውን ወዲያውኑ እረዳለሁ፡፡ ሁሉን ነገሮች አዋቂው ብዬ ብጠራህም፣ እነዚያ የዕውቀት የመጨረሻ ከፍተኛ ህልውና የሆኑት የዓላማህ ፍጥረቶችና መሣሪያዎች መሆናቸውን ማመን አለብኝ፡፡ የሟች ሰው ፍጥረት ምስጢርህን ለመፍታት ክብርህን ለመግለጽ የህላዌህን ባህርይ እንኳ ለመጠቆም ከሚችለው በላይ የተከበርክ፣ ለመገመት ከሚቻል በላይ የተከበርክ ነህ፤ እነዚህ ጥረቶች በትዕዛዝህ የተንቀሳቀሱና የአንተ ፈጠራ ውጤቶች በመሆናቸው ፣ እንዲህ ያሉት ጥረቶች ምንም አይነት ውጤት ቢያስገኙም ለፍጡራንም ከወሰንከው ገደብ የማለፍ ተስፋ ሊኖራቸው ከቶ አይችሉም፡፡ እጅግ በጣም ብፁዕ የሆኑት ቅዱሳን አንተን ለማወደስ የሚያቀርቡት ከፍተኛ ስሜት፣ እጅግ በጣም የተማሩት ሰዎች የአንተን ባህርይ ለመረዳት በመሞከር ሊናገሩት የሚችሉት እጅግ በጣም ጥልቅ ጥበብ፣ በዚያ በአንተ ሉዓላዊነት ሙሉ በሙሉ በሚገዛው፣ የአንተን ውበት በሚያስጌጠው፣ በአንተ ብዕር ኃይል በሚንቀሳቀሰው ማዕከል ዙሪያ ይሽከረከራሉ፤ አምላኬ ሆይ! በተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ ህልውናና በግልፀትህ ብዕር መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት እንዳለ የግድ የሚያመለክቱትን አይነት ቃላት ስለመናገሬ ይቅር በለኝ፡፡ እነዚያ ከአንተ ጋር ግንኙነት ያላቸው፣ ከዚህ አይነቱ የማዛመድ ሐሳብ በላይ በጣም በጣም ከፍ ያሉ ናቸው፡፡ ማንኛውም ማወዳደርና ማመሳሰል ለግልጸትህ ዛፍ ተገቢ አይደለም፡፡ የአንተን ክስተትና የውበትህን ጎሕ የመረዳት መንገድ ሁሉ ተዘግቷል፡፡ ሟች ሰው ስለ አንተ ሊናገር ወይም አንተን ሊገልጽበት የሚችለው ባህርይ ወይም አንተን ሊያወድበት የሚችለው ምስጋና ከአንተ ክብር በጣም የራቀ ይሁን! አገልጋዮችህን ያዘዝካቸው፣ የተቻላቸውን ያህል ግርማህንና ክብርህን የማወደስ ማንኛውም ምግባር፣ ለራሳቸው እጅግ ጥልቅ ሕያውነት ወደ ተሰጠው ደረጃ፣ ራሳቸውን ወደ ማወቅ ደረጃ ለመድረስ የሚያስችላቸው የእነተ ፀጋ ምልክት ብቻ ነው፡፡
በምንም ጊዜ፣ ከአንተ በስተቀር የአንተን ምስጢር ጠልቆ ለማወቅ፣ ወይም የአንተን ታቅነት በሚገባ ለማወደስ የቻለ የለም፡፡ አንተ በምርምር የማትገኝ፣ ከሰዎችም ምስጋና በላይ ሆነህ ዘለዓለም ትኖራለህ፣ የማይደረስብህ፣ ምንም የማይሳንህ፣ ሁሉን አዋቂ የቅዱሳን ቅዱስ ከሆንከው ከአንተ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡
አምላኬ ሆይ የክብሮች ክብርና ከሁሉ በላይ አንፀባራቂው ብርሃን በአንተ ላይ ይረፍ፡፡ ግርማህ በጣም የመጠቀ በመሆኑ ምንም የሰው ሃሳብ ሊደርስበት አይችልም፤ ፍጹም ኃይልህም በጣም ከፍተኛ በመሆኑ የሰዎች ልቦችና አዕምሮዎች አእዋፋት ከፍታዎቹ ላይ ለመድረስ ከቶ አይችሉም፡፡ ሕያዋን ሁሉ ለደረጃህ እንደሚገባ ሊያወድሱህ ኃይል አልባነታቸውን ይገልፃሉ፡፡ ለመገመት ከሚቻል በላይ የተከበርክ ነህ፡፡ አንተ በራስህ እንዳለህ የምታውቀው ራስህ ብቻ ስለሆንክ ህያውነትህን ሊያሞግስ፣ ወይም ከሁሉም በላይ ጥልቀ በሆነው ውስጣዊ ህልውናህ በሚገኘው ሁኔታ የበረከትህን ማስረጃዎች ጠልቆ ለመረዳት የሚችል ማንም የለም፡፡ ጌታ አምላካችን ሆይ፣ የፍጥረትንና የፈጠረን ዓለም ወደ መኖር ለጠራህበት በረከት፣ ከአንተ በቀር ሌላ ምንም በሚገባ ሊገምተው በማይችለው፣ በማነቃቂያህ ኃይል በድምቀቀት በሚያበራው ምስጋና ለአንተ ምስጋና አቀርባለሁ፡፡ ከዚህም በላይ፣ ለዚህ ቅዱስ ቡራኬ፣ ለዚህ በግልፀትና በፍጥረት መንግስቶችህ ለተገለፀው ድንቅ ምልክት ለአስፈሪ ቅርበትህና ለአሸናፊው ግርማህ ክብር እንደሚገባው አወድስሃለሁ፣ ምስጋናም አቀርብልሃለሁ፡፡ ክብር ሁሉ ለአንተ ይሁን፡፡ ያ ለአንተ የሚገባው ለመገመት ከሚቻል በላይ የተከበረ ነው፡፡ በእውነቱ የደረጃህን ምጥቀት ማንም በቂ በሆነ ሁኔታ ተረድቶት፣ ወይም ከአንተ በቀር ሌላ ማንም ለአንተ እንደሚገባ አውቆህ አያውቅም፡፡ ከአንተ በቀር ሌላ የግልፀትህን ፍተኝነት ለመገመት የሚችል የሌለ ሲሆን፣ አንተ በሰፊ በረከትህ ጎርፎች አማካይነት ትገለፃለህ፡፡ ስምህ የተወደሰ ይሁን፣ ከአንተ በቀር ሌላ ማንም የባህርይህን ፍንጭ እንኳ ለመናገር ይችል ዘንድ ነፃ ህልውና አለውን. ከአንተም በቀር ሌላው አንተን ላውቅበት የምችልበት የአምሳል ምልክት አለውን. የታወቀ ሁሉ መታወቁን የሚያገኘው፣ ከሁሉም በላይ ግልጹ ከሚለው ስምህ ውበት ነው፤ እያንዳንዱ ነገር ከማይሸነፈው ፈቃድህ በሚፈልቀው አርገብጋቢ ኃይል ከሥረ መሠረቱ ተንቀሳቅሷል፡፡ አንተ ከሁሉም ነገሮች ይበልጥ ለሁሉ ነገሮች ቅርብ ነህ፡፡ የተመሰገነንክና የተከበርክ ነህ፡፡ ምጥቀትህ እነዚያ የመረዳት ኃይልን የተለገሱት ሰዎች እጆች ወደ አንተ ለመዘርጋት ከሚችሉበት ከፍታ የላቀ ነው፤ መጨረሻ የሌለውም ጥልቀትህ የሰዎች አዕምሮዎችና የመገንዘብ ችሎታዎች ወንዞች ከዚያ ለመጉረፍ ከሚችሉበት ይበልጥ ጥልቅ ነው፡፡
አቤቱ አንተ ሩኅሩኅ ጌታ ሆይ! አንተ ለጋሱና መሐሪው ሆይ! እኛ የደጀሰላምህ አገልጋዮች ነን፤ በከለላ ሰጪውም የመለኮታዊ አንድነትህ ጥላ ስር ተሰብስበናል፡፡ የምህረትህ ፀሐይ በሁሉም ላይ ያበራል፤ የበረከትህም ደመናዎች በሁሉም ላይ ያዘንባሉ፤ ስጦታዎችህ ሁሉንም ይከባሉ፤ ፍቅራዊ አምላካዊ ጥበቃህ ሁሉን በህይወት ያኖራል፡፡ የአንተ ጥበቃ ሁሉን ይከልላል፤ የችሮታህ እይታዎችም በሁሉም ላይ ያርፋሉ፤ ጌታ ሆይ! የማያልቁትን ስጦታዎችህን ስጠን፣ የመርሖህም ብርሃን እንዲያበራ ፈቃድህ ይሁን፡፡ አይኖችን አብራ፣ ልቦችን በማያቋርጥ ሐሴት አስደስት፤ በሁሉም ሰዎች ላይ አዲስ መንፈስ ዝራ፣ ዘላለማዊ ሕይወትንም አጎናጽፋቸው፡፡ እውነተኛ ማስተዋልንም በሮች ክፈት፣ የእምነትም ብርሃን በድምቀት እንዲያበራ ፈቃድህ ይሁን፤ ሰዎች ሁሉ እንደ አንድ ፀሐይ ጨረሮች እንደ አንድ ውቅያኖስ ማዕበሎች፣ እንደ አንድ ዛፍም ፍሬዎች ይሆኑ ዘንድ፣ በቸርነትህ ጥላ ሥር ስብሰባቸው፤ እንዲስማሙና አንድ እንዲሆኑም አድርጋቸው፤ ከአንድ ምንጭ እንዲጠጡ ይሁን፤ በአንድ ልዝብ ነፋስም እንዲነቃቁ ፈቃድህ ይሁን፡፡ ከአንድ የብርሃን ምንጭም ብርሃን ይቀበሉ፡፡ አንተ ሰጪው መሐሪው ምንም የማይሳነው ነህና፡፡

bahaiprayers.net
~879w AB00065KIN

ጌታ አምላኬ ሆይ፣ ስምህ የተወደሰ ይሁን! ጨለማ እያንዳንዱን ነገር ሸፍኗል፡፡ የክፋት ኃይሎችም የሁሉንም አገር ሕዝቦች ከበዋል፤ ይሁን እንጂ በእነዚህ ውስጥ የጥበብህን ውበቶች አያለሁ የአምላካዊ ጥበቃህንም ብርሃኖች ድምቀት እለያለሁ፡፡ እነዚያ ልክ በግርዶሽ የተሸፈኑ ያህል ከአንተ የተዘጉት፣ የአንተን ብርሃን ለማጥፋት፣ እሳትህን ለማዳፋን ፣ የፀጋህም ነፋሶች እንዳይነፍሱ ለመገደብ ኃይል አለን በለው ያስባሉ፤ አይቻላቸውም ፣ ለዚሁም የአንተ ታላቅነት ይመሰክርልኛል! እያንዳንዱ መከራ የጥበብህ ማህደር፣ እያንዳንዱም ስቃይ የአምላካዊ ጥበቃህ መጓጓዣ ስለሆነ እንጂ፣ የምድርና የሰማይ ኃይሎች ሁሉ ቢያብሩብንም እንኳ፣ ማንም ደፍሮ ባልተቃወመን ነበር፤ በፊቴ በግልጽ የተዘረጉትን የጥበብህን ድንቅ ምስጢራት ሁሉ ብገልጽ ኖሮ፣ የጠላቶችህ ልጓም ዛቦች በተበጣጠሱ ነበር፡፡ ስለዚህ አምላኬ ሆይ ፣ ምስጋና ለአንተ ይሁን! እነዚያን የሚወዱህን ከፈቃድህና ከበጎ ፍላጎትህ በሚጎርፈው ሕግ ዙሪያ እንድትሰበስባቸው፤ ለልቦቻቸውም እርግጠኝነትን የሚሰጠውን እንድትልክላቸው፤ ከሁሉም በላይ ታላቅ በሆነው ስምህ እማጸንሃለሁ፡፡ አንተ የሚያስደስትህን ሁሉ ለማድረግ የማይሳንህ ነህ፣ በእውነቱ አንተ በአደጋ ጊዜ ረዳቱ፣ በገዛ ራሱም ነዋሪው ነህ፡፡ አምላኬ ሆይ፣የቀናት ንጉስ የሆነውን ቀን፣ አንተ ከሁሉ በላቁት መልእክቶችህ ውስጥ ለሕሩያንህና ለነቢያትህ የተስፋ ቃል ያበሰርክለትን ቀን፣ የስሞችህን ሁሉ ክብር ውበት በተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ ላይ ያበራህበትን ቀን ስለገለጽህ ስምህ የተመሰገነ ይሁን፤ ወደ አንተ የተመለሰ፣ አንተ ወዳለህበት የገባ የድምጽህንም ዜማዎች የሰማ ቡራኬው ታላቅ ነው፡፡ ጌታዬ ሆይ ፣ የግልፀትህ የላቁ ሐሴቶች የምድርህን ነዋሪዎች ሁሉ ነፍሶች ይሞሉ ዘንድ፤ እነዚያ ለአንተ ውድ የሆኑት ቃልህን በአገልጋዮችህ መካከል እንዲያወድሱ፣ ምስጋናህንም በፍጡራንህ መካከል እንዲያሰራጩ እንድትረዳቸው፣ በእርሱ የስሞችህ መንግስት በማምለክ በሚከበረው ስም እማፀንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ ወደ ፀጋህ የህይወት ውሃዎች ስለመራሃቸው በችሮታህ ከአንተ እንዳይከለከሉ ፈቃድህ ይሁን፣ ወደ ዙፋንህም መኖሪያ ስለጠራሃቸው፣ በፍቅራዊ ደግነትህ፣ ከቅርበትህ እንዳታባርራቸው እለምንሃለሁ፤ ከአንተ በስተቀር ከማንኛውም ነገር ሙሉ በሙሉ እንዲላቀቁ የሚያደርጋቸውን ላክላቸው፤ የጨቋኞች ማየልም ሆነ፣ የእነዚያ በአንተ ከሁሉም በላይ ክብር የተመላና ከሁሉም በላይ ታላቅ የሆነ ህልውና እናምንም ያሉት ሰዎች የሚያቀርቡአቸው ሃሳቦች ከአንተ ሊከለክሉአቸው በማይችሉበት ሁኔታ በአንተ ቅርበት ሰማይ ውስጥ እንዲበሩ አድርጋቸው፤
አቤቱ አንተ የተፈጠሩትን ነገሮች ሁሉ በትዕዛዝህ ኃይል ወደ መኖር ያመጣህ ጌታ ሆይ ክብር ለአንተ ይሁን! ጌታ ሆይ! እነዚያን ከአንተ በስተቀር ሌላውን የተውትን እርዳቸው ፣ታላቅ ድልም አቀዳጃቸው፤ ጌታ ሆይ ፣አገልጋዮችህን ለመርዳት ለማበረታትና ለማጠናከር ስኬታማም እንዲሆኑ ለማስቻል፣ ለመደገፍ ገናናነትን ክብርንና ከፍተኝነትን ለማጎናፀፍ፣ ለማበልፀግና በድንቅ ድልም አሸናፊዎች እንዲሆኑ ለማድረግ በሰማይና በምድር በመከላከላቸውም ሁሉ የሚገኙትን የመላእክት ሠራዊት ላክላቸው፤ አንተ የእነርሱ ጌታ፣ የሰማያትና የምድር ጌታ የሁሉ ዓለማት ጌታ ነህ፤ ጌታ ሆይ፣ በእነዚህ አገልጋዮችህ ኃይል፣ ይህን እምነት አጠናክረው በዓለም ህዝቦች ሁሉ ላይ የበላይነትን እንዲያገኙ አድርጋቸው፣ እነርሱ በእውነቱ ከአንተ በስተቀር ከማንኛውም ነገር ራሳቸውን ያለቀቁ አገልጋዮችህ ናቸው፤ አንተ በእርግጥ የእውነተኛ እማኞች መከታ ነህና፡፡ ጌታ ሆይ፣ በእነርሱ ለዚህ ለማይደፈረው እምነት ታማኝ መሆን አማካይነት፣ ልቦቻቸው በሰማያትና በምድር ከመካከላቸውም ከሚገኘው ከማንኛውም ነገር የበለጠ እየጠነከሩ እንዲሄዱ ፈቃድህ ይሁን፣ ጌታ ሆይ በሁሉም የሰው ዘር የተኮረ እይታ ፊት ኃይልህን ያሳዩ ዘንድ እጆቻቸውን በድንቅ ኃይልህ ምልክቶች አበርታ፤ ጌታ ሆይ ! በመንገድህ ሰማዕትነትን ስለፈለጉ ለታጋሽ አገልጋዮችህ በቀናትህ ተገቢ ድል በመፍቀድ አሸናፊዎች አድርጋቸው፡፡ ያንን ለዐዕምሮዎቻቸው መጽናናትን የሚያመጣውን ውስጣዊ ሕያውነቶቻቸው ሐሴት እንዲያደርጉ የሚያደርገውን፣ለልቦቻቸው እርግጠኝነትን ለአካሎቻቸውም መረጋጋትን የሚሰጠውንና ነፍሶቻቸውን ወደ አምላክ፣ ከሁሉም በላይ ወደተከበረው ዘንድ ለመውጣት፣ ወደ ላቀው ገነትና አንተ ለእውነተኛ የዕውቀትና የመልካም ተግባር ሰዎች ወደ አዘጋጀሃቸው የክብር አካባቢዎች ለመድረስ የሚያስችላቸውን ላክላቸው፤ በእውነቱ አንተ ሁሉን ነገሮች ታውቃለህ፤ እኛ ግን አገልጋዮችህ፣ ምርኮኞችህ ባሮችህና ምስኪኖችህ ነን፡፡ እግዚአብሄር ጌታችን ሆይ ከአንተ በቀር ሌላ ጌታ አንጠራም፣ አቤቱ አንተ ለዚህ ዓለምና ለሚቀጥለው የምህረት አምላክ የሆንክ ሆይ፣ ከአንተ በቀር ከሌላ ከማንም ቡራኬዎችን ወይም ጸጋን አንማፀንም የአንተ መላው ህያውነት የሀብት፣የነፃነት የክብር የግርማና የወሰን አልባ ፀጋ ምሳሌ ሲሆን፣ እኛ ግን የድህነት፣የኢምንትነት፣ የረዳት ቢስነትና የጥፋት መገለጫዎች ነን፡፡ ጌታ ሆይ፣ካሳችንን ከዚህና ከሚቀጥለው ዓለም መልካም ነገሮች ከሰማይ ጀምሮ ከዚያ በታች እስካለችው ምድር ከተዘረጉትም ብዙና ልዩ ልዩ ፀጋዎች ከአንተ መሠጠቱ በጣም ወደሚገባው ለውጠው፡፡ በእውነቱ አንተ ጌታችንና የሁሉ ነገሮች ጌታ ነህ፤ ከአንተ ለሆኑት ነገሮች በመጓተት፣ራሳችንን አሳልፈን ለእጅህ እንሰጣለን፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ሆይ! ከሁሉም በላይ ከፍተኛ በሆነው ተራራ ጫፍ ላይ ባለው ቅዱስ ዛፍ፣ በዚያ ምሥራቃዊም ምዕራባዊም ባልሆነ ዛፍ ውስጥ ያንን ነበልባሉ ወደ ሰማይ ሠራዊት እስኪያደርግ ድረስ የተንበለበለውን እሳት፣ ከዚያም ነበልባል፣ እነዚያ እውነታዎች የመርሐን ብርሃን የጨበጡትና በእውነቱ እኛ በደብረ ሲና ተራራ ዳገት ላይ እሳት አየን በማለት የጮሁለትን የመለኮታዊ ፍቅር እሳት ስላቀጣጠልክ ምስጋና ለአንተ ይሁን፤ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ! ከፍተኛ ነበልባሉ መላዋን ምድር ለማንቀሳቀስ እስኪችል ድረስ፣ ቀን በቀን በተተካ ቁጥር ይህ እሳት እየጨመረ እንዲሄድ አድርግ፤ አቤቱ አንተ ጌታዬ ሆይ! የፍቅርህ ብርሃን በእያንዳንዱ ልብ ውስጥ እንዲያበራ አድርግ፤ የዕውቀትህን መንፈስ በሰዎች ነፋሶች ውስጥ ተንፍስ፤ በአንድነትህ ጥቅሶች ልቦቻቸውን አስደስት፤ እነዚያን በመቃብሮቻቸው ውስጥ የሚኖሩትን ወደ ህይወት ጥራቸው፤ ትዕቢተኞችን አስጠንቀቅ፤ ደስታ መላዋን ምድር እንዲያቅፍ አድርግ፣ የጠሩ ውሃዎችን ላክልን፣ በግልጽ ውበቶች በተመላውም ጉባኤ ላይ፣ ያንን ከካምፉር ምንጭ የተበረዘውን፤ ጽዋ አዙርላቸው፤ ………

*1. ቁርአን 24፣35 *2. ኡርአን፤ 28፣29 *3. ቁርአን 76፣5

በእውነቱ አንተ ሰጪው ይቅር ባዩ፤ ምንጊዜም ለጋሱ ነህ፤ በእርግጥም አንተ መሐሪው ሩኅሩኁ ነህ፡፡ እርሱ አምላክ ነው! አቤቱ አንተ እጅግ ተወዳጄ የሆንክ ጌታ አምላክ ሆይ! እነዚህ ድምጽህን የሰሙ፣ ለቃልህ ጆሮዎቸቸውን ያቀኑ ወደ ጥሪህም ያዳመጡ አገልጋዮችህ ናቸው፡፡ በአንተ አምነዋል የአንተን ድንቅ ስራዎች አይተዋል፣ የማስረጃህን ትክክልነት ተቀብለዋ፤ ስለማረጋገጫህም መስክረዋል፤ በመንገዶችህም ተራምደዋል፤ መርሆህን ተከትለዋል፤ አንተን ምስጢራት ተረድተዋል፣ የመጽሐፍህን ድብቅ ይዘት፣ የብራናህን ጥቅሶች የመልእክቶችህንና የጽላቶችህንም አስደሳች ዜናዎች ተገንዝበዋል፡፡ በልብስህ ጠርዝ ላይ ተንጠላጥለዋል፡፡ የብርሃንህንና የታላቅነትህንም ካባ አጥብቀው ይዘዋል፡፡ እርምጃዎቻቸው በቃ- ኪዳንህ መንገድ ተጠናክረዋል፡፡ ልቦቻቸውም ለአዲሱ ሥርዓትህ ጽኑዎች ሆነዋል፡፡ ጌታ ሆይ! የመለኮታዊ መስብህን ነበልባል በልቦቻቸው ውስጥ አቀጣጥል፤ የፍቅርና የማስተዋል ወፍም ከልቦቻቸው ውስጥ እንድትዘምር ፈቃድህ ይሁን፣ አሳማኝ ምልክቶች አንፀባራቂ ሰንደቅ ዓላማዎች እንደ ቃልህም ፍጹማን እንዲሆኑ አድርጋቸው፡፡ በእነርሱ አማካይነት እምነትህ እንዲከበር የአንተ ኣርማዎች እንዲዘረጉ ድንቅ ስራዎችህም በስፋትና በጥልቀት እንዲሰራጩ፣ ቃልህም ድል እንዲነሳ አድርግ የተወዳጆችህንም ወገቦች አበርታ፤ ስምህን እንዲያወድሱ አንበቶቻቸውን አፍታታ፣የአንተንም ቅዱስ ፈቃና ፍላጎት ለመፈፀም እንዲችሉ አነቃቃቸው፤ ፊቶቻቸውን በቅዱስነት መንግስትህ ውስጥ አብራ እምነትህ ድልን እንዲጎናፀፍ ለማድረግ እንዲነሱ በመርዳት ደስታቸውን ፍጹም አድርግላቸው፡፡ ጌታ ሆይ! እኛ ደካሞች ነን፣ የቅዱስነትህን መዓዛዎች ለማሰራጨት እንድንችል አበርታን፣ ምስኪኖች ነን፤ በመለኮታዊ አንድነትህ ግምጃ-ቤቶች ውስጥ ከሚገኙት ሀብቶችህ አበልጽገን፣ የተራቆትን ነን፣ የፀጋህን ካባ ሀብቶችህ አበልጽገን፣ የተራቆትን ነን፤ የፀጋህን ካባ አልብሰን፣ኃጢአተኞች ነን፤ ኃጢአታችንን በፀጋህ በችሮታህና በይቅር ባይነትህ ይቅር በለን፡፡ በእውነቱ፣ አንተ ረዳቱ አጋዡ ፀጋ የተመላው ኃያሉ ፣ኃይል የተመላው ነህና፤ የእርሱ፣ የንዑሱ ክብር በእነዚያ ጥብቅና ፅኑዎች በሆኑት ላይ ይረፍ፡፡

bahaiprayers.net
~292w BH03908
ናውሩዝ መጋቢት 12 ቀን የባሃኢ ዓመት የመጀመሪያ ቀን እንዲሁም የደስታና የመስተንግዶ ዕለት ነው፡፡
አምላኬ ሆይ ለአንተ ፍቅር ሲሉ አንተን ከሚያስከፉ ነገሮች ሁሉ ተጠብቀው ለጾሙት የናውሩዝን ክብረ በዓል ስለሰየምክላቸው ምስጋና ለአንተ ይሁን፡፡ ጌታዬ ሆይ የአንተ ፍቅር እሳትና አንተ ባዘዝከው ፆም የተፈጠረው ግለት በእምነትህ እንዲነዱ፣ አንተንም በማመስገንና በማስታወስ የተወሰኑ እንዲሆኑ እንዲያደርጋቸው ፈቃድህ ይሁን፤ ጌታዬ ሆይ፣ አንተ ባዘዝከው ፆም ጌጥ እንዳስጌጥካቸው ሁሉ በፀጋህና ልግስና በተመላበት ደግነትህ የተቀባይነትህንም ጌጥ አጎናጽፋቸው፤ የሰዎች ሥራ ሁሉ ዋጋ የሚኖረው በአንተ መልካም ፈቃድ ሲደገፍ፤ በትዕዛዝህም ላይ ሲመሠረት ነውና አንተ ፆሙን ያላከበረውን እንደፆመ ብትቆጥረው አንዲህ ያለው ሰው ከእነዚያ ከእምቅድመ ዓለም ጀምረው ፆሙን ከአከበሩት ጋር ይቆጠራል፡፡ ፆሙን ያከበረውን እንዳልጾመ ብትመለከተው ያ ሰው የግልፀትህን ካባ በአቧራ እንዲቆሽሽ ከአደረጉትና ከዚህ ህያው ምንጭ የጠራ ውሃ እንዲወገዱ ከተደረጉት ጋር ይቆጠራል፡፡
አንተ፣ በእርሱ ፣ በስራዎቸህ ሁሉ ምስጉን ነህ የሚለው ዓርማ ከፍ የተደረገው ፤ ትዕዛዝህ ሁሉ የሚከበር ነህ ፤ የሚለውም ሰንደቅ በእርሱ አማካይነት የተዘረጋው ነህ፤ የሁሉም ነገር ልቀት በትዕዛዝህና በቃልህ ላይ ሲመሠረት ብቻ መሆኑን የእያንዳንዱም ተግባር ዋጋ በአንተ ፈቃድና በፍላጎትህ መልካም ፈቃድ እንደሚወሰን እንዲገነዘቡ፣ የሰዎችም ስራዎች ሁሉ ልጓም በአንተ ፈቃድና በትዕዛዝህ መዳፍ ውስጥ መሆኑን እንዲያውቁ፣ ይህን ደረጃህን ለአገልጋዮችህ ግለጽላቸው፣ ክርስቶስ አንተ የመንፈሱ (የየሡስ) አባት ሆይ፣ ስልጣን ሁሉ ያንተ ነው፤ በማለት በሚያወድስባቸው ፤ ወዳጅህም (መሐመድ) አንተ ከሁሉም በላይ ተወዳጅ የሆንከው ሆይ፣ ውበትህን ስለገለጽህ ከእነዚያ ከአንተ በቀር ከሌላው ሁሉ ከተላቀቁት ራሳቸውንም ወደ እርሱ አንተን ራስህን ገላጭና የባህርያትህ ክስተት ወደሆነው ካዞሩት በስተቀር ሌሎች ሰዎች ሁሉ እንዲያዝኑ ወደ ተደረጉበትወደ ታላቁ ስምህ ግልፀት ዙፋን ለመድረስ የሚያስችላቸውን ለተወዳጆችህ ስለፃፍክላቸው ክብር ላንተ ይሁን. በማለት በሚጮህባቸው በእነዚህ ቀናት ምንም ነገር ከውበትህ እንዳይጋርዳቸው ይህን እንዲያውቁ አድርጋቸው፤ ጌታዬ ሆይ፣ እርሱ የአንተ ቅርንጫፍ የሆነውና አጃቢዎችህ በሙሉ አንተን ለማስደሰት ባላቸው ጉጉት በመንበርህ ክልል ውስጥ ሆነው ፆማቸውን ከፆሙ በኋላ ዛሬ ፈስከዋል፡፡ ለእርሱም ለእነርሱም በእነዚያ ቀናት ወደ ቅርበትህ መድረክ ለገቡትም ሁሉ በመጽሐፍህ ውስጥ የወሰንከውን መልካም ነገር ሁሉ እዘዝ እዘዝላቸው፤ እንግዲህ በዚህም ህይወት በወዲያኛውም ህይወት የሚጠቅማቸውን አድላቸው፡፡ አንተ በእውነቱ ሁሉን አዋቂው ፍጹም ጠቢቡ ነህና፡፡
bahaiprayers.net
~294w BH10589
  • Naw-Ruz

ናውሩዝ መጋቢት 12 ቀን የባሃኢ ዓመት የመጀመሪያ ቀን እንዲሁም የደስታና የመስተንግዶ ዕለት ነው፡፡
አምላኬ ሆይ ለአንተ ፍቅር ሲሉ አንተን ከሚያስከፉ ነገሮች ሁሉ ተጠብቀው ለጾሙት የናውሩዝን ክብረ በዓል ስለሰየምክላቸው ምስጋና ለአንተ ይሁን፡፡ ጌታዬ ሆይ የአንተ ፍቅር እሳትና አንተ ባዘዝከው ፆም የተፈጠረው ግለት በእምነትህ እንዲነዱ፣ አንተንም በማመስገንና በማስታወስ የተወሰኑ እንዲሆኑ እንዲያደርጋቸው ፈቃድህ ይሁን፤ ጌታዬ ሆይ፣ አንተ ባዘዝከው ፆም ጌጥ እንዳስጌጥካቸው ሁሉ በፀጋህና ልግስና በተመላበት ደግነትህ የተቀባይነትህንም ጌጥ አጎናጽፋቸው፤ የሰዎች ሥራ ሁሉ ዋጋ የሚኖረው በአንተ መልካም ፈቃድ ሲደገፍ፤ በትዕዛዝህም ላይ ሲመሠረት ነውና አንተ ፆሙን ያላከበረውን እንደፆመ ብትቆጥረው አንዲህ ያለው ሰው ከእነዚያ ከእምቅድመ ዓለም ጀምረው ፆሙን ከአከበሩት ጋር ይቆጠራል፡፡ ፆሙን ያከበረውን እንዳልጾመ ብትመለከተው ያ ሰው የግልፀትህን ካባ በአቧራ እንዲቆሽሽ ከአደረጉትና ከዚህ ህያው ምንጭ የጠራ ውሃ እንዲወገዱ ከተደረጉት ጋር ይቆጠራል፡፡
አንተ፣ በእርሱ ፣ በስራዎቸህ ሁሉ ምስጉን ነህ የሚለው ዓርማ ከፍ የተደረገው ፤ ትዕዛዝህ ሁሉ የሚከበር ነህ ፤ የሚለውም ሰንደቅ በእርሱ አማካይነት የተዘረጋው ነህ፤ የሁሉም ነገር ልቀት በትዕዛዝህና በቃልህ ላይ ሲመሠረት ብቻ መሆኑን የእያንዳንዱም ተግባር ዋጋ በአንተ ፈቃድና በፍላጎትህ መልካም ፈቃድ እንደሚወሰን እንዲገነዘቡ፣ የሰዎችም ስራዎች ሁሉ ልጓም በአንተ ፈቃድና በትዕዛዝህ መዳፍ ውስጥ መሆኑን እንዲያውቁ፣ ይህን ደረጃህን ለአገልጋዮችህ ግለጽላቸው፣ ክርስቶስ አንተ የመንፈሱ (የየሡስ) አባት ሆይ፣ ስልጣን ሁሉ ያንተ ነው፤ በማለት በሚያወድስባቸው ፤ ወዳጅህም (መሐመድ) አንተ ከሁሉም በላይ ተወዳጅ የሆንከው ሆይ፣ ውበትህን ስለገለጽህ ከእነዚያ ከአንተ በቀር ከሌላው ሁሉ ከተላቀቁት ራሳቸውንም ወደ እርሱ አንተን ራስህን ገላጭና የባህርያትህ ክስተት ወደሆነው ካዞሩት በስተቀር ሌሎች ሰዎች ሁሉ እንዲያዝኑ ወደ ተደረጉበትወደ ታላቁ ስምህ ግልፀት ዙፋን ለመድረስ የሚያስችላቸውን ለተወዳጆችህ ስለፃፍክላቸው ክብር ላንተ ይሁን. በማለት በሚጮህባቸው በእነዚህ ቀናት ምንም ነገር ከውበትህ እንዳይጋርዳቸው ይህን እንዲያውቁ አድርጋቸው፤ ጌታዬ ሆይ፣ እርሱ የአንተ ቅርንጫፍ የሆነውና አጃቢዎችህ በሙሉ አንተን ለማስደሰት ባላቸው ጉጉት በመንበርህ ክልል ውስጥ ሆነው ፆማቸውን ከፆሙ በኋላ ዛሬ ፈስከዋል፡፡ ለእርሱም ለእነርሱም በእነዚያ ቀናት ወደ ቅርበትህ መድረክ ለገቡትም ሁሉ በመጽሐፍህ ውስጥ የወሰንከውን መልካም ነገር ሁሉ እዘዝ እዘዝላቸው፤ እንግዲህ በዚህም ህይወት በወዲያኛውም ህይወት የሚጠቅማቸውን አድላቸው፡፡ አንተ በእውነቱ ሁሉን አዋቂው ፍጹም ጠቢቡ ነህና፡፡

bahaiprayers.net
~81w AB10492
(በነፍሰ ጡር የሚደረግ)
ጌታዬ ሆይ! ጌታዬ ሆይ! በእውነቱ ወደ ግልጹ መንግስትህ ስለመራሃት፣ በአላፊ ጠፊውም ዓለም የአንተን ጥሪ እንድትሰማና በሁሉም ነገሮች ውስጥ የአንተን ድል አድራጊ ንግስና መከሰት የሚያረጋግጡትን ምልክቶችህን ለማየት እንድችል ስላደረግሃት ለምትለምንህና ለምትማፀንህ ባሪያህ ለትሑቷ ሴት አገልጋይህ ለለገስካት ችሮታ አወድስሃለሁ፣ ደግሜም አመሰግንሃለሁ፡፡
ጌታዬ ሆይ ይህን በማኅፀኔ ውስጥ ያለውን ለአንተ አደራ ሰጥቻለሁ፡፡ ስለዚህ በአንተ ችሮታና ቸርነት በመንግስትህ ውስጥ ተመስጋኝ ህፃንና የታደለ ነፍስ ይሆን ዘንድ፣ በአንተ ትምህርት ጥበቃ ሥር እንዲያድግና እንዲዳብር አድርገው፤ በእውነቱ አንተ ፀጋ የተመላው ነህ! በእርግጥ አንተ የታላቅ ችሮታ ጌታ ነህ!
bahaiprayers.net
~485w BB00619
  • For the Dead

እርሱ አምላክ ነው፤ እርሱ የፍቅራዊ ደግነትና የቸርነት ጌታ የሆነው የተከበረ ነው፤ አንተ ምንም የማይሳንህ ጌታ የሆንክ አምላኬ ሆይ፣ ክብር ለአንተ ይሁን፣ ምንም የማይሳንህ ስለመሆንህና ስለኃያልነትህ ስለሉዓላዊነትህና ስለፍቅራዊ ደግነትህ፣ ስለፀጋህና ስለሥልጣንህ፣ ስለሕያውነትህ አንድዬነትና ስለህላዌህ አንድነት፣ከፍጥረት ዓለምና በዚያም ከሚገኙት ሁሉ የተቀደስክና የተከበርክ ስለመሆንህ እመሠክራለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ! ከአንተ በቀር ከሁሉም ተላቅቄ አንተን አጥብቄ መያዜንና ወደ ቸርነትህ ውቅያኖስ፣ ወደ ልግስናህ ሰማይና ወደ ፀጋህ ቀኑ ኮከብ ዛሬ ታየኛለህ፡፡ ጌታ ሆይ! በአገልጋይህ ውስጥ አደራህን እንዳስቀምጥክና ይህም ለዓለም ህይወት የሰጠህበት መንፈስ መሆኑን እመሰክራለሁ፡፡ በቀናትህ የፈፀመውን ሥራ ምሕረት በተመላበት ሁኔታ እንድትቀበለው በግልፀትህ ሉል ብርሃን እለምንሃለሁ፡፡ በመልካም ፈቃድህ ክብር እንዲጎናፀፍና በአንተ ተቀባይነት እንዲያጌጥ ፈቃድህ ይሁን፡፡ ጌታዬ ሆይ! አቤቱ አንተ የሰዎች ሁሉ ጌታ ሆይ! እኔ ራሴና የተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ ስለ ኃያልነትህ እንመሰክራለን፤ ይህን ወደ አንተ ወደ መንግስተ ሰማያዊ ስፍራህ፣ ወደ ላቀው ገነትህና ወደ ቅርበትህ ማረፊያ ያረገውን መንፈስ ከአንተ ከራስህ እንዳታገልለው እለምንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ አገልጋይህ ብዕር ሊገልፃቸው አንደበትም ሊያወሳቸው በማይችል መንግስተ ሰማያዊ ሥፍራዎች ውስጥ ከሕሩያንህ፣ ከቅዱሳንህና ከመልእክተኞችህ ጋር እንዲወዳጅ ፈቃድህ ይሁን፤ ጌታዬ ሆይ፤ በእውነቱ ምስኪኑ ወደ ሀብትህ መንግስት ባይተዋሩ በክልሎችህ ውስጥ ወዳለው መኖሪያ ቤቱ እርሱ በጣም የተጠማው ወደ በረከትህ መንግስተ ሰማያዊ ወንዝ ገሥግሷል፡፡ ጌታ ሆይ ከፀጋህ ማዕድና ከበረከትህ ችሮታ ድርሻውን አትንፈገው፤ አንተ በእውነቱ ፍጹም ኃያሉ፤ ፀጋ የተመላው ፍጹም በረከት የተመላው ነህና! አምላኬ ሆይ፣ አደራህ ወደ አንተ ተመልሷል፡፡ አሁን አቀባበል ላደረግህለት እንግዳህ ስጦታዎችህንና ችሮታዎችህን ከፀጋህም ዛፍ ፍሬዎች መለገሱ በምድርና በሰማይ የሚገኙ ግዛቶችህን ከከበበው ፀጋህና በረከትህ የሚጠበቅ ነው፤ አንተ የፈቀድከውን ለማድረግ ሥልጣን አለህ፤ ከአንተ ፀጋ ከተመላው ከሁሉም በላይ በረከት ከተመላው ከሩኅሩኁ ከለጋሱ ከይቅር ባዩ ከክቡሩ ከሁሉን አዋቂው በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ጌታዬ ሆይ ሰዎች እንግዳቸውን እንዲያከብሩ እንዳዘዝካቸው እርሱ ወደ አንተ ያረገውም በእውነቱ አንተ ዘንድ እንደደረሰና ቅርበትህን እንደተቀዳጀ እመሠክራለሁ፤ እንደፀጋህና እንደቸርነትህ ተቀበለው፣ በክብርህ አገልጋዮችህን ካዘዝካቸው ተግባር ራስህም ወደ ኋላ እንደማትል፣ እርሱን በበረከትህ ገመድ ላይ የተንጠላጠለውንና ወደ ሀብትህ ጎሕ ያረገውን እንደማትነፍገው በእርግጥ አውቃለሁ፡፡ ከአንተ ከአንዱ ከአንደዬው ኃይል ከተመላው፣ ከሁሉን አዋቂው በረከት ከተመላው በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ጌታ አምላኬ ሆይ፣ ክብር ለአንተ ይሁን! እርሱን በዘላለማዊ ሉዓላዊነትህ ኃይል ያከበርከውን አታዋርደው ወደ ዘለዓለማዊ መቅደስህ እንዲገባ ያደረግኽውንም ከአንተ እንዲርቅ አታድርገው፤ አምላኬ ሆይ፣ እርሱን አንተ በጌትነትህ ጥላ ሥር የከለልከውን ከአንተ መሸሻው የነበርከውን ከአንተ ዘንድ ታባርረዋለህና እርሱን አንተ ከፍ ያደረግኽውን ታዋርደዋለህን. ወይም እርሱን አንተን ለማሰታወስ ያስቻልከውን ትረሳዋለህን? አንተ የተከበርክ፣ እጅግ በጣም የተከበርክ ነህ! አንተ ከእምቅድመ ዓለም ጀምረህ የመላው ፍጥረት ንጉሥና ዋና አንቀሳቃሹ የነበርከው ነህ፣ ለዘላለምም የተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ ጌታና ወሳኛቸው ሆነህ መኖርህን ትቀጥላለህ፤ አምላኬ ሆይ አንተ የተከበርክ ነህ ለአገልጋዮችህ ምሕረት መለገስን ብታቋርጥ ሌላ ማን ምሕረት ያደርግላቸዋል፡፡ አንተ ተወዳጆችህን ካልደረህ ፤ ሌላ ማን ሊራዳቸው ይችላል? አንተ የተከበርክ፣ ለመገመት ከሚቻል በላይ የተከበርክ ነህ! አንተ ለእውነተኝነትህ የተወደስክ ነህ፤ በአርግጥም እኛ ሁላችንም አንተን እናመልካለን፤ አንተ በፍርድህ ግልጽ ነህ፣በእውነትም እኛ ሁላችንም ለአንተ እንመሠክራለን አንተ በእርግጥ ለፀጋህ የተወደድህ ነህ፤ ከአንተ በአደጋ ጊዜ ረዳቱ፣ በገዛ ራሱ ነዋሪ ከሆንከው በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡
አምላኬ ሆይ! አቤቱ አንተ ኃጢአትን ይቅር ባዩ ስጦታዎች ሰጪው ጭንቅንም አትፊው ሆይ! በእውነቱ ሥጋዊ ልብስን ጥለው ወደ መንፈሳዊው ዓለም ያረጉትን ሁሉ ኃጢአት ይቅር ትልላቸው ዘንድ እማፀንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ ከኃጢአት ሁሉ አንፃቸው ኃዘናቸውን አስወግድላቸው፣ ጨለማውንም ወደ ብርሃን ለውጥላቸው፤ ወደ ተድላ ገነት እንዲገቡ አድርጋቸው ፍጹም ንጹህ በሆነው ውሃ እጠባቸው፤ ከሁሉም በላይ ከፍተኛ በሆነው ተራራ ላይ ያለውን ግርማህንም እንዲያዩ አድርጋቸው፤

bahaiprayers.net
~583w AB00504
  • Help

አቤቱ አምላኬ፣ ተወዳጄ ንጉሴ ፍላጎቴ ሆይ! ለአንተ የማቀርባቸውን ምስጋናዎቼን ምን አንደበት ሊያወሳቸው ይችላል. ደንታ-ቢስ ነበርኩ፣ ቀሰቀስከኝ፡፡ ከአንተ ዞሬ ነበርኩ፤ ወደ አንተ እንድመልስ በፀጋህ ረዳኽኝ፡፡ እንደሞተ ሰው ነበርኩ፤ በሕይወት ውሃ ነፍስ ዘራህብኝ፡፡ መለኮታዊው ጠባቂ ሆይ መላው ኑባሬ በፀጋህ የተገኘ ነው፤ ከቸርነትህ ውሃዎች አትንፈገው ከምህረትህም ውቅያኖስ አትከልክለው፡፡ በሁሉ ጊዜያትና በሁሉ ሁኔታዎች እንድትረዳኝና እንድትደግፈኝ ጥንታዊ ቸርነትህንም ከፀጋህ መንግስተ -ሰማይ እንድፈልግ እንድታደርገኝ እማፀንሃለሁ፡፡ በእውነቱ አንተ የጸጋ ጌታ፣ የዘለዓለማዊ መንግስት ንጉሥ ነህና፡፡ ጌታ ሆይ አንተ የተከበርክ፣ ለመገመት ከሚቻል በላይ የተከበርክ ነህ! ጠልቆ የመረዳት ችሎታ ያለው እያንዳንዱ ሰው አንተን አውቆ ለመቀበል በሚያደርገው ሙከራው በጣም መንገድ ስቷል፡፡ እያንዳንዱም የበቃ የዕውቀት ሰው ስለ አንተ በሚያደርገው ምርመራ ክፉኛ ግራ ተጋብቷል፡፡ እያንዳንዱ ማስረጃ ሊታወቅ ወደማይቻለው የአንተ ሕላዌ ለመድረስ አይችልም፡፡ እያንዳንዱም ብርሃን ከኃያልነትህ የሚያፈዝ ነፀብራቅ ውስጥ ከጭላንጭሉ ብቻ ጋር እንኳ ቢወዳደር ወደኋላ ያፈገፍግና ከአድማስ በታች ይጠልቃል፡፡ ጌታ ሆይ ፀጋ የተመላበት በረከትህንና በጎ ስጦታዎችህን አጎናጽፈኝ፣ ከክብርህ ከፍተኝነት ተገቢ የሆነውንም ፍቀድልኝ፤ ጌታዬ ሆይ ልዩ ድል ለማግኘት እንድችል እርዳኝ፡፡ የማይቀር የዓላማ ስኬት በር በፊቴ ክፈትልኝ አንተ ቃል የገባሃቸው ነገሮች በቅርብ ጊዜ እንዲደርሱ ፈቃድህ ይሁን፤ አንተ በእውነቱ በሁሉ ነገሮች ላይ ኃይል አለህ፤ አምላኬ ሆይ ልቤን በፍቅርህ የህይወት ውሃዎች አድስልኝ፤ ጌታዬ ሆይ ከለጋም ምህረትህ ጽዋ አርኪ መጠጥ ስጠኝ፡፡ ጌታዬ ሆይ በክብርህ መኖሪያ ውስጥ እንድኖር ፍቀድልኝ፣ አምላኬ ሆይ መለኮታዊ ሥውርነትህ ከተሸፈነበት ጨለማ ውስጥ እንድወጣ አድርገኝ፡፡ ለእርሱ ነቁጥ ለሆነውና ለእነዚያ እምነት ደጋፊዎች ለሆኑት ከሰጠኽው ከእያንዳንዱ መልካም ነገር ለመካፈል አስችለኝ፡፡ ከአንተ መስጠቱ የሚጠበቀውንና ለደረጃህ የሚገባውን እዘዝልኝ፤ በቅዱስ ቅርበትህ ለፈፀምኳቸው ክፉ ነገሮች በፀጋህ ይቅር በለኝ በፀጋህ አድነኝ እንጂ በፍትሕ እይታ አትመልከተኝ፤ ለክብርህ በሚገባው ሁኔታ በምህረትህ አያያዝ ያዘኝ፤ በረከት ለተመላባቸው ችሮታዎችህም የሚመጥነውን ለግሰኝ፡፡ አንተ ዘለዓለም ይቅርባዩ ንዑዱ ችሮታዎችንና ሥጦታዎችን አጎናጽፈው፣ ወሰን የሌለው ፀጋ ጌታ ነህና፡፡ በእውነቱ ከአንተ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ አንተ ሁሉ ያለው፣ ከሁሉም በላይ ከፍተኛው ነህ፡፡ እግዚአብሔር ጌታችን ሆይ ! ለአንተ ከሚያስፀይፈው ከማንኛውም ነገር በፀጋህ ጠብቀን ከአንተ መሰጠቱ ተገቢ የሆነውን ስጠን፡፡ ከሰፊ ቸርነትህ ጨምርልን፣ እንዲሁም ባርከን ለፈፀምናቸው በደሎች ይቅርታ አድርግልን፤ ኃጢአቶቻችንንም ካላያችን እጠብልን፣ ፀጋ በተመላበት ይቅር ባይነትህም ቅር በለን፡፡ በእውነቱአንተ ከሁሉም በላይ የተከበርከው፣ በጋዛ ራሱም ነዋው ነህና፡፡ ፍቅር የተመላበት አምላካዊ ጠባቂነትህ፤ በሰማያትና በምድር የተፈጠሩትን ነገሮች ሁሉ አቅፏል፡፡ ይቅር ባይነትህም ከመላው ፍጥረት አልፎ ተርፏል፡፡ ሉዓላዊነት ያንተ ነው፤ የፍጥረትና የግልፀት ዓለማት በእጅህ ናቸው፤ በቀኝ እጅህ የተፈጠሩትን ነገሮች ሁሉ ይዘሃል፣ የይቅር ባይነትህ የተመደቡ መጠኖች በመዳፍህ ውስጥ ናቸው፡፡ ከአገልጋዮችህ መካከል ለፈለግኽው ለማንኛውም ይቅር ትለዋለህ፡፡ በእውነቱ አንተ ዘለዓለም ይቅር ባዩ ሁሉን አፍቃሪው ነህ፡፡ ምንም ነገር ማንኛውም ቢሆን ከዕውቀትህ አያመልጥም፣ ከአንተ የተሰወረ ምንም ነገር የለም፡፡
እግዚአብሔር ጌታችን ሆይ! በኃያልነትህ ኃይል ተብቀን፣ በመትመም ላይ ወዳለው ድንቅ ውቅያኖስህ ለመግባት አስችለን፣ ከአንተ መፈቀዱ ተገቢ የሆነውን ፍቀድልን ፡፡ አንተ የላቀው ገዢ ኃያሉ አድራጊ፣ የተከበረው ሁሉን አፍቃሪው ነህና፤ ጌታ ሆይ! ምስኪኖች ነንና ችሮታህን ስጠን፡፡ ድሆች ነንና ከሀብትህ ውቅያኖስ አጋራን፣ ችግረኞች ነንና አጥግበን፣ የተዋረድን ነንና ክብርህን አጎናጽፈን፣ የሰማይ ዐዕዋፋትና የየብስ እንሰሶች ሁሉ ምግባቸውን በየቀኑ ከአንተ ያገኛሉ፤ ሕያዋንም ሁሉ ከአንተ ጠባቂነትና ፍቅራዊ ደግነት ይካፈላሉ፤ ይህን ደካማ ፍጡር ግሩም ፀጋህን አትንሣው በኃያልነትህም ለዚህ ምስኪን ነፍስ ቸርነትህን ስጠው፡፡ የዕለት እንጀራችንን ስጠን፣ የአንተ እንጂ የሌላ ጥገኞች እንዳንሆን ከአንተም ጋር በፍጹም እንድንቋረብ፣ በአንተም መንገድ አንድንመላለስና ምስጢርህን ለመግለጽ እንድንችል ለሕይወት የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ መጠን አብዛ፡፡ አንተ ፍጹም ኃያሉ፣ አፍቃሪና ለሰው ዘር ሁሉ አስፈላጊውን ሰጪው ነህና፡፡ ጌታ ሆይ! ደካሞች ነንና አበርታን፡፡ አምላክ ሆይ! ዕውቀት ቢስ ነንና አዋቂዎች አድርገን፡፡ ጌታ ሆይ! ድሆች ነንና ባለፀጋዎች አድርገን፡፡ አምላክ ሆይ! የሞትን ነንና የህይወት እስትንፋስ ዝራብን፡፡ ጌታ ሆይ! ውርደት ራሷን ነንና በመንግስትህ ውስጥ ክብርን አጎናጽፈን፡፡ ጌታ ሆይ አንተ ከረዳኽን እንደሚያበሩት ከዋክብት እንሆናለን፡፡ አንተ ካልረዳኽን ግን ከአፈር በታች እንሆናለን፡፡ ጌታ ሆይ አበርታን፡፡ አምላክ ሆይ! ድል አጎናጽፈን፡፡ አምላክ ሆይ! እኔነትን ለማሸነፍና ከከንቱ ምኞት በላይ ለመሆን አስችለን፡፡ ጌታ ሆይ! ከዓለማዊ ቁራኛነት አድነን፤ ጌታ ሆይ! አንተን ለማገልገል እንድንነሣሣ፣ ለአንተ መስገድ ተግባራችን በመንግስትህም ውስጥ ተሳትፎአችን በሙሉ ልብ እንዲሆን በቅዱስ መንፈስ እስትንፋስ አንቃን፡፡ ጌታ ሆይ! አንተ ኃይል የተመላው ነህ1 አምላክ ሆይ፤ አንተ ይቅር-ባዩ ነህ! ጌታ ሆይ ፣ አንተ ሩኅሩኁ ነህ!

bahaiprayers.net
Also in: hy en haw hu ja
~942w BH00987

*በሃያ አራት ሰዓት ጊዜ ውስጥ አንዱ የሚደገረግ፣ ይህን ፀሎት ለመድገም የሚሻ ይቁምና ልቦናውን ወደ እግዚአብሔየር ያቅና፣ በሥፍራውም እንደቆመ የሩኅሩኁን የይቅር -ባዩን አምላክ ምሕረት እንደሚጠባበቅ ሁሉ ወደ ቀኝና ወደ ግራ ይመልከት፤ ከዚያም እንዲህ ይበል፤ *አቤቱ አንተ የስሞች ሁሉ ጌታና የሰማያት ፈጣሪ የሆንከው ሆይ! ፀሎቴ፣ ውበትህን እንዳላይ የጋረደኝን ግርዶሽ የሚያነድ እሳትና፣ ወደ ሕልውናህም ውቅያኖስ የሚመራኝ ብርሃን እንዲሆን፣ በእነዚያ ፣ ፍጹም የተከበረው የንዑዱና ሊታይ የማይቻለው አንተ ሕልውና ጎሕ በሆኑት እማፀንሃለሁ፤ *ቀጥሎም እግዚአብሔር የተባረከና የተከበረ ይሁንና፣ እጆቹን ወደ እርሱ በልመና በማንሳት እንዲህ ይበል፤ አቤቱ አንተ የዓለም እሾትና የብሔሮች ሁሉ ተወዳጅ የሆንከው ሆይ! ወደ አንተ ዞሬ፣ ከአንተ በቀር ከማንኛውም ቁራኛነት ሁሉ ተላቅቄ በእንቅስቃሴው መላው ፍጥረት በተቀሰቀሰበት ገመድህ ላይ ተንጠላጥዬ ታየኛለህ፡፡ ጌታዬ ሆይ እኔ አገልጋይህ የአገልጋይህም ልጅ ነኝ፡፡ ፈቃድንህና ፍላጎትህን ለመፈፀም ዝግጁ ሆኜ መቆሜንና ከበጎ ፈቃድህም በስቀር ሌላ እንደማልሻ ተመልከተኝ፤ አገልጋይህን እንደፈቀድከውና እንደሻህ እንድታደርገው በምሕረትህ ውቅያኖስና በጸጋህ የቀኑ ኮከብ (የዘመኑ ፀሐይ) እማጠንሃለሁ፡፡ ከመነገርና ከመወደስ በላይ በጣም ከፍ ባለው ኃያልነትህ! በአንተ የተገለፀ ማንኛውም ነገር የልቤ ፍላጎትና የነፍሴ ተወዳጅ ነው፤ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ! ሰማያትንና ምድርን የከበበውን ፈቃድህን ተመልከት እንጂ ምኖቶቼንና አድራጎቶቼን አትመልከት፣ በፍጹም ታላቁ ስምህ አቤቱ አንተ የብሔሮች ሁሉ ጌታ ሆይ አንተ የፈለግኽውን ብቻ ፈልጌአለሁ፤ የምታፈቅረውንም ብቻ አፈቅራለሁ፡፡ ከዚያም በኋላ ተንበርክኮ ግንባሩን ወደ መሬት በመድፋት እንዲህ ይበል፡፡ ከራስህ ገለፃ በቀር ከማንም ገለፃ፣ ከአንተም የመረዳት ችሎታ በቀር ከማንም የመረዳት ችሎታ በላይ የላቅህ ነህ፡፡ *ቀጥሎም ይቁምና እንዲህ ይበል፤ *ጌታዬ ሆይ ፀሎቴን ሉዓላዊነትህ እስካለ ድረስ ለመኖርና በዓለማትህም እያንዳንዱ ዓለም ስምህን ላወሳበት የምችልበት፣ የህይወት ውሃዎች ምንጭ አደርግልኝ፤ *እንደገና በመማፀን እጆቹን ወደላይ በማንሳት እንዲህ ይበል፤ አቤቱ ከአንተ ሲለቀዩ ልቦችና ነፍሶች የቀለጡ በፍቅርህም እሳት መላው ዓለም የተቀጣጠለው ሆይ! አቤቱ አንተ በሰዎች ሁሉ ላይ ገዥ የሆንከው ሆይ! በአንተ ዘንድ የሚገኘውን እንዳትነፍገኝ፣ መላውን ፍጥረት ባንበረከክህበት ስምህ እማጠንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ ይህ ባይተዋር በግርማህ ከለላ ሥር በምህረትህ ክልል ውስጥ ወዳለው፣ እጅግ በጣም ወደ ተከበረው ቤቱ ሲገሰግስ፣ ይህ ኃጢአተኛ የይቅር ባይነትህን ውቅያኖስ ይህ ዝቅተኛ የክብርህን መንበር፣ ይህ ምስኪን ፍጡር የሀብትህን ምንች ሲሻ ትመለከታለህ፤ የፈቀድከውን ማንኛውንም ነገር የማዘዝ ስልጣን ያንተ ነው፡፡ በሥራዎችህ መመስገን፣ ለትዕዛዞችህም ታዛዥነትን ማግኘት፣ ትዕዛዝ በመስጠጥም ገደብ የሌለብህ ሆነህ ፀንተህ የምትኖር መሆንህን እመሰክራለሁ፡፡ ቀጥሎም እጆቹን ወደላይ በማንሳት ከሁሉ በላይ ታላቁን ስም፣ ማለትም አላህ ኡ አብሃ (አምላ ፍጹም ክቡር) የሚለውን ሶስት ጊዜ ይደጋግም፡፡ አምላክ ይክበር ይመስገንና በእርሱ ፊት አንጎብሶ እጆቹን ጉልበቶቹ ላይ በማሳረፍ እንዲህ ይበል፤ አምላኬ ሆይ ፣ አንተን ለማምለክ በመናፈቁ አንተን ለማስታወስና ለማሞገስ በጣም በመመኘቱ መንፈሴ በመላው አካላቴ ውስጥ እንዴት እንደተንቀሳቀሰ ለዚያ በቃልህ መንግስትና በዕውቀትህ ሰማይ ትዕዛዝህ ልሳን ለመሠከረለትም መንፈሴ እንዴት እንደሚመሠክር ታያለህ፡፡ አቤቱ ጌታዬ በዚህ ሁኔታ የእኔን ምስኪንነት እንዳሳይና የአንተን በረከቶችና ፀጋዎች እንዳወሳ፣ የእኔን ደካማነት እንድመሠክርና የአንተን ሥልጣንና ኃያልነት እንድገልጽ፣ ከአንተ ጋር ያለውን ሁሉ ከአንተ መለመን እወዳለሁ፡፡ *ቀጥሎም ይቁም፣ በመማፀንም እጆቹን ሁለቱ ወደ ላይ ያንሳና እንዲህ ይበል፤ ከአንተ ከፍጹም ኃያሉ፣ ከፍጹም ለጋሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ በመጀመሪያም ሆነ በመጨረሻ ሁሉን ደንጋጊ ከሆንከው፤ ከአንተ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ በመጀመሪያም ሆነ በመቸረሻ ሁሉን ደንጋጊ ከሆንከው ከአንተ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ! ቅርታህ ድፍረትን ሰጥቶኛል፣ ምሕረትህ አጠንክሮኛል፣ ጥሪህ ቀስቅሶኛል ፀጋህም አስነስቶ ወደ አንተ መርቶኛል፡፡ እንግዲያውማ በቅርበትህ ከተማ በር ላይ ልቆም ከፈቃድህ ሰማይ ወደሚያበሩት ብርሃኖች ፊቴን ለመመለስ የምደፍር እኔ ማን ነኝ? ጌታዬ ሆይ፣ ይህ ጎስቋላ ፍጡር የፀጋህን በር ሲያንኳኳ ይህ ኢምንት ነፍስ ከበረከትህ እጆች ዘለዓለማዊውን የሕይወት ጅረት ሲሻ ትመለከታለህ፡፡ አቤቱ አንተ የስሞች ሁሉ ጌታ ሆይ፣ ትዕዛዝ ምንጊዜም ያንተው ነው፣ አቤቱ የሰማያት ፈጣሪ ሆይ የእኔ ግን ሁሉንም መተውና ለፈቃድህ በውዴታ መገዛት ነው፡፡ *ቀጥሎም እጆቹን ሶስቱ ወደ ላይ በማንሣት እንዲህ ይበል፤ እግዚአብሔር ከታላቅ ሁሉ ይበልጥ ታላቅ ነው፡፡ *ቀጥሎም ተምበርክኮ ግምባሩን ወደ መሬት በመድፋት እንዲህ ይበል፤ ወደ አንተ የቀረቡት የሚያቀርቡት ምስጋና ወደ ቅርበትህ ሰማይ ከመውጣት ወይም የእነዚያ ለአንተ ያደሩት ሰዎች ልቦች አፅዋፋት ወደ መንበርህ በር ከመድረስ በጣም ከፍ ያልክ ነህ፤ አንተ ከባህርያት ሁሉ የነፃህ ከስሞችም ሁሉ በላይ ቅዱስ መሆንህን እመሠክራለሁ:: ከአንተ ፍጹም ከላቀው ከንዑዱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ *ቀጥሎም ይቀመጥና እንዲህ ይበል፡- የተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ ፣ የሰማይ ሰራዊት የገነት አርያም ነዋዎች ከእነዚህም በላይ ከፍጹም ደማቁ አድማስ የታላቁ አንደበት ራሱም የሚመሠክሩልህ፣ አንተ አምላክ መሆንህንና ከአንተም በስተቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ ፣ እርሱም ያ የተከሰተው በእርሱም አማካይነት ሁ እና ን (ሁን) ፊደላት የተገናኙበትና የተጣመሩበት፣ ሥውሩ ምስጢር፣ ብርቁ ምልክት መሆኑን እመሰክራለሁ፡፡ ስሙ ከሁሉም በላይ ከፍተኛ በሆነው ብዕር የሠፈረው፣ በአምላክ መፃሕፍትም ውስጥ የተጠቀሰው፣ የሰማይና የምድር ዙፋን ጌታ እርሱ መሆኑን እመሰክራለሁ፡፡ *ቀጥሎም ቀጥ ብሎ ይቁምና እንዲህ ይበል፤ አቤቱ የፍጡራን ሁሉ ጌታና የሚታዩትም የማይታዩትም ነገሮች ሁሉ ባለቤት ሆይ! አንተ እምባዬንና የማሰማውን ሲቃ እነሆ ታስታውላለህ፤ የማቃሰቴን ድምፅ፣ ዋይታዬን የልቤንም ሰቆቃ ትሰማለህ፡፡ በኃያልነትህ ሕግ ተላላፊነቴ ወደ አንተ ከመቅረብ አግዶኛል፡፡ ኃጢአቴም ከቅድስናህ መንበር አግልሎኛል፤ አቤቱ ጌታዬ ፍቅርህ አበልጽጎኛል፤ ከአንተም መለየት አጥፍቶኛል፤ ከአንተ መራቅም ጨርሶኛል፡፡ በውበትህ ላይ ለማተኮርና በመጽሐፍህ ውስጥ ያሉትን ሁሉ ለማክበር እንድችል እንድትወስንልኝ በዚህ ምድረበዳ ባሉት ዱካዎችህ በዳር አልባ ስፋት ውስጥ እዚህ ነኝ፡፡ እዚህ ነኝ በሚሉት የሕሩያንህ ቃላት፣በግልፀትህ እስትንፋስናበክስተትህ የንጋት ልዝብ ነፋስ እማጠንሃለሁ፡፡ *ቀጥሎም ከሁሉም በላይ ታላቁን ስም ሶስት ጊዜ ይድገምና አጎንብሶ እጆቹን በጉልበቶቹ ላይ በማሳረፍ እንዲህ ይበል፤ አምላኬ ሆይ፣ አንተን እንዳስታውስና እንዳወድስህ ስለረዳኽኝ፣ እርሱን የምልክቶችህ ጎሕ የሆነውን ስላሳወቅኽኝ፣ በጌታነትህም ፊት እንድሰግድ ስለአደረግኽኝ፣ በአምላክነትህም ፊት ራሴን ዝቅ እንዳደርግና በታላቅነትህም አንደበት የተነገረውን ለመቀበል ስለአበቃኽኝ ምስጋና ለአንተ ይሁን፤ ከዚያም ይቁምና እንዲህ ይበል፤ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ! ጀርባዬ በኃጢአቴ ክብደት ጎብጧል፣ ግዴለሽነቴም አውድሞኛል፡፡ የእኔን ርኩስ ድርጊቶችና የአንተን ደግነት ባሰላሰልኩ ቁጥር ልቤ በውስጤ ይቀልጣል፣ ደሜም በስሮቼ ውስጥ ይፈላል፡፡ በውበትህም አቤቱ አንተ የዓለም እሾት ሆይ! ፊቴን ወደ አንተ ለማቅናት እፍረት ይሰማኛል፣ ናፋቂ እጆቼም ወደ ቸርነትህ ሰማይ ለመዘርጋት ያፍራሉ፤ አቤቱ አንተ የሰማዩና የምድሩ ዙፋን ጌታ የሆንክ አምላክ ሆይ! እንባዎቼ አንተን ከማስታወስና የአንተንም ባህርያት ከማወደስ እንዴት እንዳገዱኝ እነሆ ታያለህ! አቤቱ አንተ የፍጡራን ሁሉ ጌታ፣ የሚታዩና የማይታዩ ነገሮች ሁሉ ንጉሥ የሆንከው ሆይ! ለተወዳጆችህ እንደልግስናህና እንደፀጋህ መጠን እንድታደርግላቸው በመንግስትህ ምልክቶችና በመግዛትህ ምሥጢራት እማጠንሃለሁ፡፡ ቀጥሎም ከሁሉም በላይ ታላቁን ስም ሶስቱ ይደገምና ተንበርክኮ ግንባሩን ወደ መሬት በመድፋት እንዲህ ይላል፡፡ አምላካችን ሆይ ወደ አንተ የሚያቀርበንንና በመፃሕፍትህና በቅዱሳት ጽሁፎችህ ውስጥ ያሉትን መልካም ነገሮች የሚያድለንን ስለላክህልን ምስጋና ለአንተ ይሁን፣ አቤቱ ጌታዬ ሆይ ከዋጋ ቢስ ሃሳብና ከከንቱ አስተሳሰብ አጀቦች እንድትጠብቀን እንማፀንሃለን፡፡ በእውነቱ አንተ ኃያሉ ሁሉን አዋቂው ነህና፡፡

  • ቀጥሎም ራሱን ቀና አድርጎ ይቀመጥና እንዲህ ይበል፤ አምላኬ ሆይ፣ ሕሩያንህ የመሠከሩትን እመሠክራለሁ፣ የገነት አርያም ነዋሪዎችም በኃያሉ ዙፋንህ ዙሪያ የከበቡት ሁሉ ያረጋገጡትንም አረጋግጣለሁ፡፡ አቤቱ የዓለማት ጌታ ሆይ የሰማይና የምድር መንግስታት የአንተ ናቸው፡፡ በየዕለቱ በሃያ አራት ሰዓት ጊዜ ውስጥ አንዴ 95 ጊዜ የሚደገም፤
bahaiprayers.net
~262w BH03447
በየዕለቱ ጧት እኩለ ቀንና ማታ የሚደረግ፣ ለመፀለይ የሚሻ ሁሉ እጁን ይታጠብ በመታጠብም ላይ ሳለ እንዲህ ይበል፡፡ አምላኬ ሆይ፤ መጽሐፍህን አጥብቆ እንዲይዝና የዓለምም አጀቦች በላዩ ላይ ኃይል እንዳይኖራቸው፣ እጄን አበርታ፡፡ የእርሱም ባልሆነው በማንኛውም ነገር ውስጥ እንዳይገባ ጠብቀው፡፡ በእውነቱ አንተ ፍጹም ኃያሉ፣ ከሁሉም በላይ ኃይል የተመላው ነህና፡፡ ቀጥሎ ፊቱን በመታጠብ ላይ እያለ እንዲህ ይበል፡፡ ጌታዬ ሆይ ፊቴን ወደ አንተ መልሻለሁ! በገጽህ ብርሃን አብራው፡፡ ወደ አንተም በቀር ወደ ማንም እንዳይዞር ጠብቀው፡፡
*ከዚያም ይቁም፣ ፊቱን ወደ ቂብሊሀ የውዳሴ ማዕከል ማለትም ወደ ባህጂ አቶር በመመለስ እንዲህ ይበል፤ ከእግዚአብሔር በስተቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ ራሱ ይመሰክራል፡፡ የግልጽነትና የፍጥረት መንግስታት የእርሱ ናቸው፡፡ እርሱ በእውነቱ የግልፀት ጎህ የሆነውን በሲና ላይ የተነጋገረውን በእርሱም አማካይነት የላቀው አድማስ እንዲያበራ የተደረገውን፣ በእርሱም ሊታለፍ የማይቻለው የለውጥ ዛፍ የተናገረውን በእርሱም አማኝነት በሰማይና በምድር ላሉት ሁሉ፣ እነሆ የሁሉ ባለቤት የሆነው መጥቷል፡፡ ምድርና ሰማይ፣ ክብርና ግዛት የሰዎች ሁሉ ጌታ የላይኛውና የምድር ዙፋን ባለቤት የሆነው የአምላክ ናቸው፡፡ የሚለው ጥሪ የታወጀበትን ከስቶታል፡፡ *ከዚያም ያጎንብስና እጆቹን በጉልበቶቹ ላይ በማሳረፍ እንዲህ ይበል፤ አንተ ከእኔ ሙገሣና ከማንም ሰው ሙገሣ በላይ ከእኔ ገለፃና በሰማይና በምድር ካሉት ሁሉ ገለፃ በላይ የተከበርክ ነህ፡፡ *ከዚያም ቆሞ እጆቹን በመዘርጋት መዳፎቹንም ወደላይና ወደፊት በማቅናት እንዲህ ይበል፤ አምላኬ ሆይ፣ እርሱን በተማፃኘ ጣቶቹ በምሕረትህና በፀጋህ ዘርፍ ላይ የተንጠላጠለውን ቅር አታሰኘው፣ አቤቱ አንተ ምሕረትን ከሚያሳዩ ሁሉ ፍጹም መሐሪው ነህና! *ከዚያም ይቀመጥና እንዲህ ይበል፤ አንድነትህህና አንድዬነትህን አንተ አምላክ መሆንህን፣ ከአንተም በስተቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ፤ በእውነቱ አንተ እምነትህን ገልፀሃል፣ ቃል-ኪዳንህንም አሟልተሃል፣ በሰማይ ውስጥና በምድር ላይ ለሚኖሩትም ሁሉ የፀጋህን በር በሰፊው ከፍተሃል፤ የዓለም ለውጦችና አጋጣሚዎች ወደ አንተ ከመመለስ ሊያደናቅፋአቸው ያልቻሉ፣ እና በአንተ ዘንድ ያለውን ለማግኘት ተስፋ በማድረግ ያላቸውን ሁሉ በሰውት በተወዳጆችህ ላይ ቡራኬና ሰላም፣ ሰላምታና ክብር ይረፍ፤ በእውነቱ አንተ ምንጊዜም ይቅር-ባዩ ፍጹም ፀጋ የተመላው ነህና፤
bahaiprayers.net
~280w AB00728MDS
ጌታ አምላኬ ሆይ አንተ የተከበርክ ነህ! ለእኔና የአንተን ገጽ ለማየት ለፈለጉት ሁሉ ከቸርነትህና በረከት ከተመላበት ፀጋህ መስጠቱ የሚጠበቀውን ከስጦታዎችህና ከችሮታዎችህ መለገሱም ተገቢ የሆነውን እንድትልክልን በኃይል በሚነፍሱት የፀጋህ ነፋሶች በእነዚያም በዓላማህ ንጋቶችና በመንፈሳዊ የእውቀት ብልጭታህ የንጋት ሥፍራዎች በሆኑት እማፀንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ÷ እኔ ምስኪንና ጉስቁል ነኝ! በሀብትህ ውቅያኖስ ውስጥ አስጥመኝ፣ የተጠማሁ ነኝ ከፍቅራዊ ደግነትህ የህይወት ውሃዎች እንድጠጣ አድርገኝ፤ አገልጋችህን ፀጋ በተመላበት አምላካዊ ጥበቃህ ዛፍ ጥላ ሥር በአንድ ላይ እንድትሰበስባቸው÷ በአንተው በራስህና በእርሱ የአንተ የራስህ ህልውና ክስተትና በሰማይና በምድር ለሚገኙት ሁሉ ክፉውን ከበጎ የሚለይ ቃልህ አድርገህ በሰየምከው እማፀንሃለሁ፡፡ ከፍሬዎቹ እንዲሳተፉ ÷ወደቅጠሎቹ መንኮሻኮሽ÷ከቅርንጫፎቹ ላይ ወደሚያዜመውም ወፍ ድምጽ ጣፋጭነት ጆሮዎቻቸውን እንዲያቀኑ እርዳቸው፡፡ በእውነቱ÷ አንተ በአደጋ ጊዜ ረዳቱ÷ የማይደረስበቱ÷ ፍጹም ኃያሉ÷ ከሁሉም በላይ ፀጋ የተመላው ነህና፤
አቤቱ አንተ መሐሪው አምላክ ሆይ! አቤቱ አንተ ኃያልና ሃይል የተመላው ሆይ! አቤቱ አንተ ከሁሉም በላይ ለጋስ አባት ሆይ! እነዚህ አገልጋዮች ወደ አንተ ተመልሰው በአንተ ደጀሰላም ለመማፀን÷ ከአንተ ታላቅ መተማመኛ የአንተን የማያልቁ በረከቶች ለመለመን በአንድ ላይ ተሰባስበዋል፡፡ እነርሱ ከአንተ መልካም ደስታ በስተቀር ሌላ ዓላማ የላቸውም፡፡ የሰውን ዘር ዓለም ከማገልገል በስተቀር ሌላ ዕቅድ የላቸውም፡፡
አምላክ ሆይ! ይህን ስብሰባ ብሩህ አድርገው ልቦችን መሐሪዎች አድርጋቸው፡፡ የቅዱስ መንፈስን በረከቶች አውርድላቸው፤ የመንግስተ ሰማይ ኃይል አጎናጽፋቸው፣የመንግስተ ሰማይ አእምሮዎች በመስጠት ባርካቸው፤ በሙሉ ትሕትናና ፀፀት በተመላበት ልብ ወደ አንተ መንግስት በመመለስና ለሰው ዘር ዓለም አገልግሎት በመስጠት ሥራ እንዲጠመዱ ቅንነታቸውን አብዛ፡፡ እያንዳንዱ ብሩህ ሻማ ይሁን፡፡ እያንዳንዱ አንፀባራቂ ኮከብ ይሁን፡፡ እያንዳንዱ በአምላክ መንግስት ውስጥ ውበት የተመላ ቀለምና አስደሳች መዓዛ ያለው ይሁን፡፡ አቤቱ አንተ ለጋስ አባት ሆይ !ቡራኬዎችህን አጎናጽፈን፣ ጉድለቶቻችንን አትመልከት፡፡ በጥበቃህ መጠለያ ሥር ጠልለን፡፡ ኃጢአቶቻችንን አትመልከት፡፡ በምሕረትህ ፈውሰን እኛ ደካሞች ነን አንተ ግን ኃያል ነህ፡፡ እኛ ምስኪኖች ነንሀ አንተ ግን ሀብታም ነህ፡፡ እኛ ሕሙማን ነን፤አንተ ደግሞ ሐኪም ነህ፡፡ እኛ ችግረኞች ነን አንተ ግን ከሁሉ በላይ ቸር ነህ፡፡ አምላክ ሆይ! ሀብትህን አጎናጽፈን፡፡ አንተ ኃይል የተመላው ነህ፡፡ አንተ ሰጪው ነህ አንተ ለጋሱ ነህ፡፡
bahaiprayers.net
Also in: bi bs ca nl en ht hu kl no pl pt ro sk sl
~247w BH07775
አምላኬ፣ ጌታዬ ፣የልቤ ዓላማ ሆይ! ይህ አገልጋይህ እንክብካቤህንና ጥበቃህን በመማፀን በምሕረትህ ጥላ ሥር ሊተኛ በፀጋህም ከለላ ሥር ሊያርፍ ይፈልጋል፡፡
ጌታዬ ሆይ አንተን ብቻ እንጂ ሌላውን ነገር ሁሉ እንዳያዩ አይኖቼን እንቅልፍ ከቶ በማያታልለው አይንህ እንድትጠብቅልኝ እለምንሃለሁ፡፡ አይኖቼ ያንተን ምልክቶች ለማየትና የግልፀትህን አድማስ ለመመልከት እንዲችሉ የማየት ኃይላቸውን አበርታ.. አንተ በእርሱ ሁሉን ቻይነት መገለፅ ፊት የሥልጣን ሕልውና የተንቀጠቀጠለት ነህና፡፡ ከአንተ ከፍፁም ኃያሉ ከሁሉን አስገባሪው ከማይገታው በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እግዚአብሄር አምላኬ ሆይ፣ አንተን የሚናፍቁት ከአንተ በመለየታቸው ምክንያት አይኖቻቸው ሳያንቀላፉ እኔ እንዴት መተኛትን መምረጥ እችላለሁ፤ የተወዳጆችህም ነፍሶች ከአጠገብህ በጣም በመራቃቸው ክፉኛ አዝነው እያሉ እንዴት ለማረፍ እጋደማለሁ. ጌታዬ ሆይ ፣ መንፈሴንና መላውን ህያውነቴን ለቀኙ እጅህ ኃይልና ጥበቃ አደራ ሰጥቻለሁ፡፡ እራሴን በአንተ ኃይል ትራሴ ላይ አሳርፋለሁ፡፡ በአንተ ፍላጎትና መልካም ፈቃድ አቀናዋለሁ፡፡ በእውነቱ አንተ አኑዋሪው ጠባቂው ፍፁም ኃያሉና ከሁሉም በላይ ኃይል የተመላው ነህ፡፡
በኃያልነትህ ! ተኝቼም ሆነ ነቅቼ አንተ ከምትፈልገው በስተቀር ሌላ አልጠይቅም፡፡ እኔ አገልጋይህና በመዳፎችህ ውስጥ ያለሁ ነኝ፡፡ የመልካም ፈቃድህን መዓዛ ለማወድ የሚችል ተግባር ለመፈፀም እንድንችል በፀጋህ እርዳኝ፡፡ በእውነቱ የእኔና የእነዚያ ወደ አንተ የመቅረቤ ዕድል የተሰጣቸው ምኖት ይህ ነውና፡፡ የዓለማት ጌታ ሆይ ምስጋና ለአንተ ይሁን! አንተ አውነትን ፈላጊ ሆይ እግዚአብሔር አይንህን እንዲከፍትልህ ከፈለግህ በእኩለ ሌሊት እግዚአብሔር መማፀን እንዲህ በማለት ወደ እርሱ መፀለይና ከእርሱ ጋር መቋረብ አለብህ፡፡ ጌታ ሆይ ÷ ፊቴን ወደ አንድነትህ መንግስት በመመለስ በምሕረትህ ባህር ውስጥ ሰጥሜአለሁ ፡፡ ጌታ ሆይ በዚህ ጨለማ ሌሊት እይታዬ የአንተን ብርሃኖች በማየት እንዲበራ አድርግልኝ በዚህም ድንቅ ዘመን በፍቅርህ ወይን ጠጅ አስደስተኝ ፡፡ ጌታ ሆይ የክብርህን ብርሃን እንዳይና ወደ ውበትህ እንድሳብ፣ ጥሪህን እንድሰማ አድርገኝ የመንግስተ ሰማይህንም በሮች በፊት ለፊቴ ክፈትልኝ፡፡ በእውነቱ አንተ ሰጪው ለጋሱ መሐሪው ይቅር ባዩ ነህና፡፡
bahaiprayers.net
~148w BB00018DET
  • Pioneers

አምላኬ ሆይ የአንተን መልካም ደስታ ከመቀዳጀት ለአንተ አገልጋይ ለመሆን ተቀባይነት ስለማግኘቴ ማረጋገጫን ከማግኘት፣ ለአንተ አገልግሎት ለማበርከት ዓላማ ራሴን ከመስጠት፣ በአንተ ታላቅ የወይን እርሻ ውስጥ ከመሥራትና ሁሉንም ነገር በአንተ መንገድ መስዋዕት ከማድረግ በስተቀር በልቤ ውስጥ ምንም አይነት ሌላ ፍላጎት እንደሌለ አንተ የምታውቀውና ምስክሬም ነህ፡፡ አንተ ሁሉን አዋቂው፤ ሁሉን የሚያየው ነህና ለአንተ ካለኝ ፍቅር፤ እርምጃዎቼን ወደ ተራሮችና ወደ በረሃዎች በማቅናት አንተ መንግስት ስለመምጣቱ ክፍለ ባለ ድምጽ ከማወጅ በሰዎችም ሁሉ መካከል ጥሪህን ከማሰማት በስተቀር ሌላ ምኞት የለኝም፡፡ አምላክ ሆይ! ለዚህ ረዳት ለሌለው መንገዱን ክፈትለት፣ ለዚህ ህመምተኛ መድኃኒት ፈቀድለት፣ ለዚህም ለሚሰቃየው ፈውስህን አውርድለት ፡፡ ልቤ እየነደደ ፣ ከአይኖቼም እንባ እየጎረፈ በአንተ ደጀሰላም ላይ ሆኜ እማፀንሃለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ በመንገድህ ማንኛውንም መከራ ለመቻል ዝግጁ ነኝ፣ በሙሉ ልቤና ነፍሴም ማንኛውንም ችግር ለመቋቋም እመኛለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ! ከፈተናዎች ጠብቀኝ፤ እኔ ከሁሉም ነገሮች ፊቴን ማዞሬንና ረሴን ከሁሉም ሃሳቦች ነፃ ማድረግን አንተ ደህና አድርገህ ታውቃለህ፡፡ አንተን ከማንሳት በስተቀር ምንም ሥራ፣ አንተን ከማገልገልም በቀር ሌላ ምንም ምኖት የለኝም፡፡

bahaiprayers.net
~758w BHU0004SUF
  • Protection

ጌታ አምላኬ ሆይ፣ስምህ የተወደሰ ይሁን! ወደ አንተ ተመልሰው የአንተን እምነት ለረዱት አገልጋዮችህ ልቦቻቸውን የሚያስደስተውን ከምሕረትህ መንግስተ ሰማይና ፍቅር ከተመላበት የአንተ የርኅራኄ ደመናዎች እንድታዘንብላቸው፣ ሰዓቱ በደረሰበት፣ ትንሳኤውም በተፈፀመበት፣ ፍርሐትና መንቀጥቀጥም በእነዚያ በሰማይ በሚገኙት ሁሉ፣ በምድር ላይ በሚገኙትም ሁሉ ላይ በወረደበት ስምህ እማፀንሃለሁ፡፡ ጌታ ሆይ፣ ወንድ አገልጋዮችህንና ሴት አገልጋዮችህን ከእውነት የራቁ እምነቶችና የከንቱ አስተሳሰቦች ጦሮች ሊያደርሱባቸው ከሚችሉት አደጋዎች እንድትጠብቃቸው፣ ከፀጋህም እጆች በለዘብታ የሚወርዱትን የዕውቀትህን ውሃዎች መጠጥ እንድትሰጣቸው እለምንሃለሁ፡፡ አንተ በእውነቱ ፍጹም ኃያሉ፣ ከሁሉ በላይ የተከበረው ፣ ዘላለም ይቅር ባዩ፣ ከሁሉም በላይ ለጋሱ ነህና፡፡ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ! የፍቅርህን ገመድ አጥብቄ በመያዝ፣ ራሴንም ሙሉ በሙሉ ለአንተ እንክብካቤና ለጥበቃህ በመስጠት ከቤቴ ወጥቻለሁ፡፡ ተወዳጆችህን ከእነዚያ ከትክክለኛው መንገድ ከራቁትና ከጠማማዎቹ፣ ከእያንዳንዱም አመፀኛ ጨቋኝ፤‹ ከእያንዳንዱም ከአንተ የራቀ ክፉ አድራጊ በጠበቅህበት ኃይልህ፣ እኔንም በቸርነትህና በፀጋህ ከማንኛውም አደጋ እንድትጠብቀኝ እማፀንሃለሁ፡፡ በስልጣንህና በኃያልነትህም በደህና ወደቤቴ ለመመለስ አስችለኝ፡፡ በእርግጥ አንተ ፍጹም ኃያሉ፣ በአደጋ ጊዜ ረዳቱ፣ በገዛ ራሱም ነዋሪው ነህና፡፡
አምላኬ ሆይ! ማናቸውንም ፈቃዴን ሁሉ አንተ በቅዱስ ጽላትህ ላይ በፃፍከው መሠረት እንድወስን፣ በገዥነትህ ስልጣን ካዘዝከው ውጭ የሆነውን ምኞት ሁሉ እንዳልመኝ፣ በፈቃድህም ካዘዝክልኝ ዕድል በስተቀር የሌላ ፍላጎት ከቶ እንዳያድርብኝ፣ ግርማው ሰማይንና ምድርን በከበበው ስምህ እለምንሃለሁ፡፡ በል እግዚአብሔር ሁሉን ነገሮች ከሁሉም በላይ ያረካል፣ በሰማይና በምድር ከእግዚአብሐየር በስተቀር የሚያረካ የለም፣ በእውነቱ እርሱ በራሱ አዋቂው ህይወት ሰጪው ምንም የማይሳነው ነው፡፡ ጌታዬ ሆይ! የሁሉን ነገሮች አስቀድሞ የታዘዘ በእጅህ መዳፍ ውስጥ ይዘሃልና፣ ለእኔና ለእነዚያ ለሚያምኑብህ፣ ያንን በእናንተ መጽሐፍ ውስጥ እንደሠፈረው በአንተ ግመት ይበልጥ፤እንደሚጠቅመን ያሰብከውን እዘዝልን፡፡ ነልካም ሥጦታዎችህ በእነዚያ ፍቅርህን በሚወዱት ላይ ያለማቋረጥ ይዘንባሉ፣ የመንግስተ ሰማያዊ በረከቶችህም ድንቅ ምልክቶች፣ ለእነዚያ መለኮታ አንድነትህን ለተቀበሉት በበቂ መጠን ይሰጣሉ፡፡ ለእኛ ያዘጋጀሀልንን ማንኛውንም ነገር ለጥበቃ ለአንተ እንሰጣለን፣ እውቀትህ የሚያቅፈውንም መልካም ነገረ ለጥበቃ ለአንተ እንሰጣለን፤ ዕውቀትህ የሚያቅፈውንም መልካም ነገር ሁሉ እንድትሰጠኝ እንማፀናለሁ፡፡ ጌታ ሆይ ፣ ሁሉን አዋቂነት ከሚያየው ክፉ ነገር ሁሉ ጠብቀን ኃይላና ብርታት በአንተ እንጂ በሌላ የለምና፣ ድል አድራጊነትም ከአንተ ዘንድ በቀር ከሌላ አይመጣምና፣ ማዘዙም የአንተ ብቻ ነው፤ እግዚአብሔር የፈቀደው ማንኛውም ነገር ሆኗል፤ እርሱ ያልፈቀደውም አይሆንም፡፡ ከሁሉም በላይ በተከበረው፣ በፍጹም ኃያሉ አምላክ በቀር በሌላ ኃይልም ብርታትም የለም፡፡ አምላክ ሆይ፣ ክብር ለአንተ ይሁን! አንተ ከሁሉ ነገሮች በፊት የነበርክ፣ ከሁሉ ነገሮች በኋላ የምትኖርና ከሁሉም ነገሮች በኋላም አልፈህ የምትቆይ አምላክ ነህ፡፡ አንተ ሁሉን ነገሮች የሚያውቀው፣ በሁሉ ነገሮችም ላይ የላቀ የበላይ የሆነው አምላክ ነህ፡፡ አንተ ሁሉን ነገሮች በምሕረት የምትዳሰሰው፣ በሁሉ ነገሮችም መካከል የሚፈርደው፣ የማየት ኃይሉም ሁሉን ነገሮች የሚያቅፈው አምላክ ነህ፤ አንተ አምላክ ጌታዬ ነህ፣ አንተ ስለሁኔታዬ ታውቃለህ፡፡ አንተ ውስጣዊውንና ውጫዊውን ህያውነቴን ታያለህ፡፡ ለእኔና ለጥሪህ መልስ ለሰጡት አማኞች ይቅር ባይነትህን ስጠን፣ ኃዘን ሊያደርስብኝ ከሚፈልግ ወይም ክፉ ከሚመኝልኝ ከማንኛውም ሰው ጉዳት የሚከላከልልኝ አርኪ ረዳቴ ሁን፡፡ በእውነቱ አንተ የተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ ጌታ ነህ፡፡ አንተ እያንዳንዱን ሰው ታረካለህ፤ ነገር ግን ማንም ያለ አንተ እርዳታ ራሱን የሚችል ለመሆን አይችልም፡፡ በስመ እግዚአብሔር በሚያርበደብደው ግርማ ጌታ በሁሉን አስገዳጁ! የገዢነት ምንጭ በእጁ ውስጥ ያለው ጌታ የተቀደሰ ይሁን፡፡ እርሱ “ሁን” ሲል በሚሆነው የትዕዛዝ ቃሉ የፈቀደውን ማንኛውንም ነገር ይፈጥራል የሥልጣን ኃይል ከዚህ በፊት የእርሱ ነበር፣ ለወደፊቱም የእርሱ መሆኑን ይቀጥላል፡፡ እርሱ የፈለገውን ማንኛውንም ሰው በትዕዛዙ ፍጹም ኃይል ድል አድራጊ ያደርገዋል፡፡ እርሱ በእውነቱ ኃይል የተመላው ፣ ፍጹም ኃይሉ ነው፡፡ በግልፀትና በፍጥረት ዓለማት በመካከላቸውም በሚገኘው በማንኛውም ውስጥ ክብርና ግርማ ሁሉ የእርሱ ናቸው፡፡ በእውነቱ እርሱ ምንም የማይሳነው፣ ንዑዱ ነው፤ ከእምቅድመ ዓለም ጀምሮ እርሱ የማይበገር ሃይል ምንጭ ነበር፡፡ በዚህም ሁኔታ ለዘለዓለም ይኖራል፡፡ እርሱ በእርግጥ ኃያልነትና የስልጣን ጌታ ነው፡፡ በሰማይና በምድር በመካከላቸውም የሚገኙት ዓለማት ሁሉ የአምላክ ናቸው፡፡ ስልጣኑም በሁሉም ነገሮች ላይ የላቀ የበላይ ነው፡፡ የምድርና የሰማይ ሀብት ሁሉ፣ በመካከላቸውም የሚገኙት ነገሮች ሁሉ የእርሱ ናቸው፡፡ ጥበቃውም በሁሉም ነገሮች ላይ ተዘርግቶ ይገኛል፡፡ እርሱ የሰማያጥና የምድር፣ በመካከላቸውም የሚገኝ የማንኛውም ነገር ፈጣሪ ነው፡፡ በእውነቱ እርሱ በሁሉ ነገሮች ላይ ምስክር ነው፡፡ እር በሰማያትና በምድር የሚኖሩትን፣ እንዲሁም በመካከላቸው የሚያገኙትን ሁሉ ስለሥራቸው የሚጠይቅ ጌታ ነው፤ በእውነቱ እግዚአብሔር ስለተሠሩት ስራዎች ለመጠየቅ ፈጣን ነው፡፡ እርሱ በሰማያትና በምድር በመካከላቸውም ለሚገኘው ሁሉ የተመደበውን ድርሻ መጠን ይወስናል፡፡ በእውነቱ እርሱ የላቀው ጠባቂ ነው፡፡ እርሱ የሰማይንና የምድርን በመካከላቸውም የሚገኘውን ነገር ሁሉ ቁልፎች በመዳፉ ውስጥ ይይዛል፡፡ እርሱ በገዛ ራሱ ፍላጎት፣ በራሱ ትዕዛዝ ስጦታዎችን ይሰጣል፡፡ በእርግጥ ፀጋው ሁሉን ያቅፋል፣ እንዲሁም እርሱ ሁሉን አዋቂው ነው፡፡ በል፤ እግዚአብሔር ለእኔ አርኪዬ ነው፣ እርሱ የሁሉንም ነገሮች ዓለም በመዳፉ ውስጥ የያዘው ነው፡፡ በሰማያትና በምድር በመካከላቸውም በሚገኙት የእርሱ ሠራዊት ኃይል፣ ከአገልጋዮቹ መካከል የፈለገውን ማንኛውንም ሰው ይጠብቃል፡፡ በእውነቱ እግዚአብሔር ሁሉንም ነገሮች ይጠብቃል፡፡ ጌታ ሆይ ለመገመት ከሚቻል በላይ የተከበርክ ነህ! በፊት ለፊታችንና ከበስተኋላችን፣ ከእራሶቻችን በላይ፣ ከበስተቀኛችን ከበስተግራችን ከእግሮቻችን በታችና በተጋለጥንበት በእያንዳንዱ ሌላ ጎን በኩል ከሚገኘው ከማንኛውም ነገር ጠብቀን፤ በእውነቱ አንተ ጥበቃ ከሁሉም ነገሮች ላይ አይቋረጥም፡፡ ጌታዬ ሆይ ህዝቦች ሁሉ በጭንቅና በመከራ፣ በልፋትና በችግር የተከበቡ መሆናቸውን አንተ ታውቃለህ፡፡ እያንዳንዱን ሰው ልዩ ልዩ ፈተና ይገጥመዋል፣ የእባብ ንክሻን የመሰለ አደገኛ ችግርም ይደርስበታል፣ ተከላካይነትና ጠባቂነት ከተመላው ከአንተ ክንፍ በስተቀር ሰው ሌላ መጠጊያና መሸሻ የለውም፡፡ አቤቱ አንተ መሐሪው አምላክ ሆይ ጌታዬ ሆይ ጠባቂነትህን የብረት ልብሴ፣ ክብካቤህን ጋሻዬ በአንተ አነድነት ደጅ ላይ ትህትና ማሳየቴን ጠባቂዬ፣ ተከላካይነትህንና መከታተነትህን ምሽጌና መኖሪያዬ አድርግልኝ፡፡ ለራሴና ለምኞቴ ቅድሚያ ከመስጠት ጠብቀኝ፤ ከማንኛውም ሕመም፣ ፈተና ችግርና ጭንቀት አድነኝ፡፡ በእውነቱ አንተ ጠባቂው ሞግዚቱ፣ በህይወት የሚያቆየው፣ አርኪው ነህና በእርግጥም አንተ ከሁሉ በላይ መሐሪዎች ከሆኑት ሁሉ በላይ ፈጹም መሐሪው ነህና፡፡

bahaiprayers.net
Short Obligatory Prayer ~112w BH11209

*‹‹ዕለታዊ የግዴታ ፀሎቶች በቁጥር ሶስት ናቸው፡፡ ምዕመኑ ከእነዚህ ከሶስቱ ፀሎቶች የፈለገውን እንዱን ለመምረጥ ሙሉ በሙሉ ነፃ ነው፤ ግን ከእነዚህ አንዱን አብረውት በሚሄዱት መመሪያዎች መሠረት የመድገም ግዴታ አለበት፡፡

*የግዴታ ፀሎቶች ትህትናንና ታዛዥነትን የሚጋብዙና፣ ሰው ፊቱን ወደ እግዚአብሔር በመመለስ ለእርሱ ምሀላ እንዲያወርብ የሚረዱት በመሆናቸው በየዕለቱ መደገማቸው ግዴታ ነው፤ እንዲህ ባሉት ፀሎቶችም አማካይነት የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት ይፈጥራል፣ ወደ እርሱም ለመቅረብ ይሻል፣ ከእውነተኛ የልቡ ፍቅረኛም ጋር ይነጋገራል፣ እንዲሁም መንፈሳዊ ደረጃዎችን ይቀዳጃል፣

ይህ ፀሎት በየዕለቱ ከቀትር እስከ ፀሐይ መጥለቂያ ባለው ጊዜ ውስጥ አንዴ የሚደረግ ነው፤ አምላኬ ሆይ አንተን እንዳውቅና እንድሰግድልህ እንደፈጠርከኝ እመሰክራለሁ፡፡ በዚህች ሰዓት የእኔን ደካማነትና የአንተን ኃያልነት የእኔን ምስኪንነትና የአንተን ሀብታምነት አረጋግጣለሁ፡፡ ከአንተ በአደጋ ጊዜ ረዳት፣ በገዛ ራሱም ነዋሪ ከሆንከው በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡

bahaiprayers.net
~470w BH02023
  • Steadfastness

ስምህ የተከበረ ይሁን አምላኬ ሆይ! ለአንተ ባለን ፍቅርና ለፈቃድህ በታዛዥነታችን ለመጽናት እታዎቻችንን በአንተ ፊት ላይ ለማተኮርና ክብርህን ለማወደስ እንድታስችለን፤ የተፈጠሩትን ነገሮች ሁሉ በከበበው ሥልጣንህ ከመላው ፍጥረት ልቆ በሚገኘው ሉዓላዊነትህ፣ በጥበብህ ውስጥ በተደበቀውና ምድርህንና ሰማይህን በፈጠርክበት ቃልህ እማጠንሃለሁ፡፡አምላኬ ሆይ የአንተን ምልክቶች በፍጡራንህ መካከል በሰፊው ለማሰራጨት፣ በመንግስትህም ውስጥ እምነትህን ለመጠበቅ፤ የሚያስችለንን ኃይል ስጠን፤ ከፍጡራንህ መካከል ማንኛውም ስምህን ሳያነሣ ራስህን ችለህ ዘለዓለም ኖረሃል፡፡ከእምቅድመ ዓለም ጀምረህ በነበርክበት ሁኔታ ዘለዓለም ትኖራለህ፡፡ ፍፁም እምነቴን በአንተ አኑሬአለሁ፡፡ ፊቴንም ወደ አንተ መልሼአለሁ፡፡ በፍቅራዊ ጥበቃህ ገመድ ላይ ተንጠላጥያለሁ፣ ወደ ምሕረትህም ጥላ ገስግሼአለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ ተስፋው እንደተቀጨበት ሰው ከደጅህ አውጥተህ አትጣለኝ፤ አንተን ብቻ ስለምሻ ፀጋህን አትንሳኝ፤ ከአንተ ከዘለዓለም ይቅር ባዩ- ከሁሉም በላይ ለጋሱ በስተቀር ሌላ አምላክየለምና፡፡ አቤቱ ላወቁህ ሁሉ ተወዳጅ የሆንከው ሆይ ለአንተ ምስጋና ይድረስህ! የፀጋና የምህረት ጌታ የሆንክ አምላክ ሆይ! አንተ በትዕዛዝ ቃሉ መላው ፍጥረት ወደመኖር የተጠራበት ንጉስ ነህ፤ የአገልጋዮቹ ተግባሮች ፀጋውን ከመለገስ ያልገቱት የቸርነቱንም መገለፅ ሊያስቀሩ ያልቻሉት ፍጹም ቸር ጌታ ነህ፤ ይህ አገልጋይህ በአለሞችህ እያንዳንዱ ዓለም የደህንነቱ ምክንያት የሆነውን እንዲያገኝ ታደርገው ዘንድ እማፀንሃለሁ፡፡ አንተ በእውነቱ ፍፁም ኃያሉ ከሁሉም በላይ ኃይል የተመላው ሁሉን አዋቂው ፍጹም ጠቢቡ ነህና፡፡ ከሁሉም በላይ ተወዳጄ የሆንክ ጌታ ሆይ፣ ምስጋና ለአንተ ይሁን! በእምነትህ ጽኑ አድርገኝ፣ ከእነዚያ ቃል- ኪዳንህን ካልጠሱት፣የራሳቸውን ከእውነት የራቁ ከንቱ እምነቶችና ጣኦቶች ካልተከተሉትም ጋር እንድቆጠር ፈቃድህ ይሁን በአንተ ዘንድ የእውነት መቀመጫ ለማግኘት አስችለኝ፣ የምህረትህንም ምልክት አጎናጽፈኝ፣ ከእነዚያም ምንም ፍርሐት ከማይኖርባቸው፣ በኃዘንም ላይ ከማይጣሉት አገልጋዮችህ ጋር እንድቀላቀል አድርገኝ፣ ጌታዬ ሆይ ለራሴ አትተወኝ፣ እርሱን የአንተ የራስህ ክስተት የሆነውን ከማወቅ አትንፈገኝ፣ ከእነዚያ ከአንተ ቅዱስ መንበር ፊቶቻቸውን ከአዞሩትም ጋር አትቁጠረኝ፡፡ አምላኬ ሆይ ፣ ከእነዚያ ውበትህን አትኩረው ለማየት ከታደሱት፣ በዚያም ትልቅ ደስታን የሚደሰቱ በመሆናቸው፣ የዚያችን ትንሷን ጊዜ እንኳ በሰማያትና በምድር መንግስታት ግዛት ወይም በመላው ፍጥረት ዓለም ከማይለውጡት ጋር ቁጠረኝ ጌታ ሆይ የምድሩን ህዝቦች በአሳዛኝ ሁኔታ በተሳሳቱባቸው በእነዚህ ቀናት በእኔ ላይ ምሕረት ይኑርህ፡፡ አምላኬ ሆይ ስለዚህ ያንን በአንተ አስተሳሰብ ተገቢ የሆነውን ለግሰኘ፡፡ በእውነቱ አንተ ፍጹም ኃይል የተሞላው ፀጋ የተሞላው በረከት የተመላው፣ዘለዓለም ይቅር ባይ ነህና፡፡ አምላኬ ሆይ ከእነዚህ ጆሮዎቻቸው ከደነቆሩት፣ አይኖቻቸው ከታወሩት፣ አንደበታቸው ንግግር አልባ ከሆኑት ልቦቻቸው መገንዘብ ከተሳናቸው ጋር እንዳልቆጠር ፍቃድህ ይሁን፡፡ ጌታ ሆይ ከድንቁርናና ከራስ ወዳድነት ፍላጎት እሳት አድነን ወደ ላቀው ምህረትህም ክልል እንድገባ አድርገኝ፡፡ ያንን ለሕሩያንን ያዘዝከውንም በላዬ አውርድልኝ፡፡ የፈለግኽውን ለማድረግ ችሎታዬ ያለህ ነህና፡፡ በእውነቱ አንተ በአደጋ ጊዜ እረዳቱ በገዛ ራሱ ነዋሪው ነህ፡፡ አቤቱ አምላኬ ሆይ የተመሰገንክና የተወደስክ ነህ ወደ ቅዱስ ቅርበትህ የመድረስ መቀደጃው ቀን በፍጥነት እንዲቃረብ ፈቃድህ ይሁን፡፡ በፍቅርህና በመልካም ደስታ ኃይል ልቦቻችንን አስደስትልን ለፍላጎትህና ለትዕዛዝህም በፈቃደኝነት እንድገዛ ጽኑመትን አጎናጽፈን፡፡ በእውነቱ እውቀትን የፈጠርካቸውንና የምትፈጥራቸውን ነገሮች ሁሉ ያቅፋል፡፡ የመንግስተ ሰማይ የሆነው ሃያልነትህን ወደ መኖር ከጠራኽንና ከምትጠራው ከማንኛውም ነገር ይልቃል፡፡ ከአንተ በቀር የሚሰገድለት ማንም የለም፡፡ ከአንተ በቀር የሚፈለግ ማንም የለም፣ካንተ በቀር የሚመለክ ማንም የለም፡፡ በበጎ ፈቃድህም ፈቃድህም በቀር ምንም የሚወደድ የለም፡፡ በእውነቱ አንተ ከሁሉ በላይ ከፍተኛው ገዥ የላቀ እውነት በአደጋ ጊዜ እረዳቱ በገዛ ራሱ ነዋሪው ነህና፡፡ ጌታ ሆይ አምላኬ ሆይ! ተወዳጆችህ በእምነትህ እንዲጠነክሩ፣ በመንገድህ እንዲራመዱ፣ በሃይማኖትህ እንዲፀኑ እርዳቸው ፡፡ እኔነትንና የብርቱ ስሜት ውርጂብኝ ወረራን ለመቋቋምና የመለኮታዊ መርሖን ብርሃን ለመከተል የሚያስችላቸውን ጸጋህን ስጣቸው፡፡ አንተ ኃይል የተመላው ፣ፀጋ የተመላው በገዛ ራሱ ነዋው ለጋሱ፣ሩኅሩኁ፣ ፍጹም ኃያሉ፣ፍጹም በረከት የተመላው ነህና፡፡

bahaiprayers.net
~206w ABU0023UNI
አምላኬ ሆይ! አምላኬ ሆይ! የአገልጋዮችህን ልብ አስተባብር፤ ታላቁን ዓላማህንም ግለጽላቸው፤ ትዕዛዝህን ይከተሉ፣ በሕግህም ይኖሩ ዘንድ፣ አምላክ ሆይ በጥረታቸው እርዳታቸው ለአንተም እንዲያገለግሉ ኃይልን ስጣቸው፣ አምላክ ሆይ! ራሳቸውን ለራሳቸው አትተው፤ እርምጃቸውን ሁሉ በዕውቀት ብርሃን ምራው፣ በፍቅርህም ልቦቻቸው አስደስት፡፡ በእውነቱ አንተ ረዳታቸውና ጌታቸው ነህና፡፡ የአንድነት ብርሃን መላዋን ዓለም እንዲያለብሱና “መንግስት የአምላክ ናት ” የሚለውም ማኅተም በሕዝቦቿ ሁሉ ግንባር ላይ እንዲታተም የአምላክ ፈቃድ ይሁን፡፡ አምላክ ሆይ! አምላኬ ሆይ! በእውነቱ ምህረቶችህ ሁሉ በእነዚህ ነፍሶች ላይ እንዲወርዱ አንተን በመጠየቅ እለምንሃለሁ፡፡ በደጀ ሰላምህ ፊት ሆኜ እማፀንሃለሁ፣ ለችሮታህና ለእውነትህ ምረጣቸው፡ ጌታ ሆይ! ልቦችን በማስተባበር አስተሳስራቸው፣ ነፍሶችን ሁሉ በስምምነት አጣምራቸው፣ መንፈሶችንም በቅዱስነትህና በአንድነትህ ምልክቶች አስደስታቸው፤ ጌታ ሆይ! እነዚህን ፊቶች በአንድነት ብርሃን አማካይነት ብሩህ አድርጋቸው፡፡ ለመንግስትህ እንዲያገለግሉ የአገልጋዮችህን ሽንጦች አጠንክርላቸው፡፡ አቤቱ አንተ ወሰን የሌለው ምሕረት ባለቤት የሆንከው ጌታ ሆይ! አቤቱ የኃጢአት ስርየትና የይቅርታ ጌታ ሆይ! ኃጢአቶቻችንን አስተሰርይልን ስለጉድለቶቻችንም ይቅርታ አድርግልን፣ ወደ ኃያልነትና ወደ ሥልጣን መንግስት በመፀለይ በመንበርህ ቅርበት ትሑታን፣ በማስረጃዎችህም ክብር ፊት ታዛዦች በመሆን ወደ ምህረትህ መንግሥት ፊቶቻችንን እንድንመልስ አድርገን፡፡ አቤቱ ጌታ አምላክ ሆይ! በፍቅርህ በረከት እንደ ባህር ማዕበሎች እንደ አትክልት ሥፍራ አበቦች የተባበርንና የተስማማን እንድንሆን አድርገን፡፡ ጌታ ሆይ! በአንድነትህ ምልክቶች አማካይነት ልቦችን አስፋቸው፣ የሰው ዘርንም ሁሉ ከአንድ አይነት የክብር ከፍታ እንደሚያበሩ ከዋክብት፣ በሕይወት ዛፍህ ላይ እንደሚያድጉ ፍጹማን ፍሬዎች አድርጋቸው፡፡ በእውነቱ፣ አንተ ፍጹም ኃይሉ፣ በገዛ ራሱ ነዋሪ፣ ሰጪው ይቅር ባዩ መሐሪው ሁሉን አዋቂው አንድዬው ፈጣሪ ነህና፡፡
bahaiprayers.net
~208w AB10703RAD
ጌታ ሆይ ! ይህን ወጣት ብሩህ አድርገው፤ በዚህ ምስኪን ፍጡር ላይ በረከትህን አውርድ፤ ዕውቀትን ለግሰው በየዕለቱም ጥዋት ተጨማሪ ጉልበት ስጠው፤ ክስሕተት ነፃ ይሆን ዘንድ፣ ለእምነትህ አገልግሎት ራሱን ይሰጥ ዘንድ የተሳሳቱትን እንዲመልስ ዕድለ ቢሶቹንም እንዲመራ ምርኮኞቹን ነፃ እንዲያወጣ ግዴለሾቹንም እንዲያነቃቃና ሁሉም አንተን በማስታወስና በማወደስ ይባረኩ ዘንድ በጥበቃህ መጠለያ ውስጥ ጠብቀው፡፡ አንተ ኃያሉና በሁሉ ላይ ስልጣን ያለው ነህና፡፡ አቤቱ አንተ ሩኅሩህ ጌታ ሆይ! ለዚህች የመንግስተ ሰማይ ልጅ መለኮታዊ ማረጋገጫን ለማግሳት በእምነትህ ጠንካራና ፅኑ ሆና ትኖር ዘንድ፣ ልክ በምስሥጢራት የጽጌረዳ አትክልት ሥፍራ እንደምትገኝም ዘማሪ ወፍ፣ በአብሃ መንግስት በእጅግ በጣም ድንቅ ድምጽ ዜማዎችን ታዜም ዘንድ፣ በዚህም ለእያንዳንዱ ሰው ደስታን ታመጣ ዘንድ፣ በፀጋህ እርዳታ በመንግስተ ሰማይ ሴት ልጆች መካከል ከፍ አድርጋት፣ ለዘለዓለማዊው ሕይወትም አብቃት፤ አንተ ለጋዙ ሁሉን አፍቃሪው ነህና፣ አቤቱ አንተ ከሁሉም በላይ ክብር የተመላህ ጌታ ሆይ ይህችን የአንተን ትንሽ ሴት አገልጋይ ብሩክና ደስተኛ አድርጋት፣በታላቅ ደስታና በከፍተኛ ሐሴት የተመላች በመሆን ጣፋጭ ሽታ ያለው መዓዛ ታሰራጭ ዘንድ በአንድነትህ ደጀሰላም የተወደደች እንድትሆንና ከፍቅርህ ጽዋ እስትረካ እንድትጠጣ አድርጋት፣ አንተ ኃያሉና ኃይል የተመላው ነህና፣ አንተ ሁሉን አዋቂው፣ ሁሉን የሚያየው ነህና፤ ጌታ ሆይ! ይህቺን የእግዚአብሔር መንግስት ልጅ በሁለቱም ዓለማት የተከበረች እንድትሆን እርዳት፣ ከዚህ ከጠፊ የትቢያ ዓለምና ልቦቻቸውን በዚያ ላይ ከአሳረፉት ፊቷን እንድታዞር አድርጋት ከሞት አልባ ዓለም ጋር ግንኙነትና ጥብቅ ትስስር ያላት ለመሆን አስችላት፤ አንተን ለማገልገል ትነሣ ዘንድ መንግስተ ሰማያዊ ኃይል ስጣት፣ በመንፈስ ቅዱስ እስትንፋሶችም አጠንክራት፤ አንተ ኃያሉ ነህ፤
bahaiprayers.net
~435w AB10244
  • Assemblies

ፍጹም ኃይል የተመላው በፀጋው የላቀ ድል ለማግኘት እንድትችሉ ይረዳችሁ ዘንድ ወደ መንፈሳዊ ጉባኤው ክፍል በምትገቡበት ጊዜ፣ በእግዚአብሔር ፍቅር በሚርገበገብ ልብና እርሱን ከማስታወስ በቀር ከሌላ ነገር ሁሉ በነፃ አንደበት ይሁን ፀሎት አድርጉ፡፡ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ ! እኛ በዚህ ታላቅ ቀን ከአንተ በቀር ከሁሉም ተላቅቀን ወደ ቅዱስ ገጽህ በፍቅር የተመለስን አገልጋዮችህ ነን፡፡ በሰው ዘር መካከል ቃልህን ከፍ ለማድረግ ባለን የዓላማ ስምምነት በአመለካከታችንና በአስተሳሰባችን ተዋሕደን በዚህ መንፈሳዊ ጉባኤ ተሰብስበናል፡፡ ጌታ አምላካችን ሆይ! የአንተ መለኮታዊ መርሖ ምልክቶች፣ በሰዎችም መካከል የላቀው እምነትህ ሰንደቅ ዓላማዎች፣ ለኃይሉ ቃል ኪዳንህም አገልጋዮች እንድንሆን አንተ ከሁሉም የላቅህ ጌታችን ሆይ በአብሀ መንግስትህን የመለኮታዊ አንድነትህ መገለጫዎች፣ በሁሉም አካባቢዎች ላይ የሚያበሩ አንፀባራቂ ከዋክብትም አድርገን፡፡ ጌታ ሆይ! በአስገራሚው ፀጋህ ሞገድ የሚንቀሳቀሱ ባሕሮች ፍፁም ክብር ከተመሉት ከፍታዎች የሚጎርፉ ጅረቶች፣ በመንግስጠ ሰማያዊው እምነት ዛፍ ላይ ያሉ መልካም ፍሬዎችና በመለኮታዊ የወይን እርሻህ ውስጥ በፀጋህ ልዝብ ነፋሶች የሚወዛወዙ ዛፎች እንድንሆን እርዳን፤ አምላክ ሆይ! አስተሳሰቦቻችን አመለካከቶቻችንና ስሜቶቻችን ልክ የአንድነት መንፈስ ይገልፁ ዘንድ ልክ እንደ አንድ ባህር ሰንበሮች አንድ እንድንሆንና እንደ አንፀባራቂው ብርሃንህ ጨረሮች በአንድነት እንድንጣመር፣ ነፍሶቻችን ለመለኮታዊ አንድነትህ ጥቅሶች እንዲገዙ ልቦቻችንም በጸጋህ ጎርፎች እንዲደሰቱ አድርጋቸው፡፡ አንተ ፀጋ የተመላው ለጋሱ ሰጪው ፍጹም ኃያሉ መሐሪው ሩኅሩህ ነህና፡፡ አቤቱ አንተ ሩኅሩህ አምላክ ሆይ! በዚህ መንፈሳዊ ጉባኤ በታላቅ ትሕትና በአንድ ላይ ተሰባስበናል፡፡ አንድ እንድንሆንና እንድንስማማ፣ እርስ በርሳችንም እንድማርና ወተት በጣፈጠ ግንኙነት እንድንቀራረብ፣ ለሰውም ዘር አንድነት መንግስት ምጹዓት ምክንያት እንድንሆን ፊቶቻችንን ወደ አንተ መንግስት በመመለስ ማረጋገጫህንና እርዳታህን እንለምናለን፡፡ ምኖታችን እንዲፈፀምልን በንፁህ ልብና በብሩህ መንፈስ ወደ አንተ እንድንፀልይና እንድንለምንህ እርዳን፡፡ ፍጹም ኃያሉ ሆይ! በፀጋህና በቸርነትህ ተመልክተን እንጂ ኃጢአታችንን አትመልከት፡፡ ጉድለቶቻችንን ይቅር በለን፡፡ በረከትህን አውርድልን፡፡ የፍቅርህን እሳት አቀጣጥለህ የአጉል ምልኮን የስሜትንና የምኖትንን ግርዶሽ አቃጥለህ አጥፋቸው ከእኔነት ድክመት ተከላክለህ ጠብቀን በመሐሪነትህ ዛፍ ጥላ ሥር ከልለን፣ የመንፈስንም ፀጥታና ዕረፍት ስጠን፡፡ በእውነቱ አንተ ኃይል የተመላው ፣ኃያሉ ነህና፡፡ በመንፈሳዊ ጉባኤ ስብሰባ መዝጊያ ላይ የሚደረግ ፀሎት አምላክ ሆይ! አምላክ ሆይ! እኛ በአንተ አምነን፣ኪዳንህና በአዲሱ ሥርዓትህ ፀንተን፣ ወደ አንተ ተስበን፣ በፍቅርህ እሳት ተቀጣጥለን፣ የእምነትህም ቅን እማኖች ሆነን በዚህ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ ተሰባስበን መገኘታችንን ከማይታየው የአንድነትህ መንግስት ተመልከተን፤ እና በአንተ የወይን እርሻ ውስጥ በማገልገል ላይ የምንገኝ፣ ሃይማኖትህን አስፋፊዎች ራሳችንን ለአንተ አገልግሎት የሰጠን የአንተ ገጽታ አምላኪዎች ለተወዳጆችህ ትሁታን፣ በበርህም ፊት ታዛዦች የሆንን፣ ሕሩያንህን በማገልገል ተግባራችንም ተቀባይነት ማግኘታችንን እንድታረጋግጥልን በማይታዩት ሠራዊቶችህም እንድትደግፈን ለአንተ ለምናበረክተውም አገልግሎት ሽንጦቻችንን እንድታጠናክርልን ለትዕዛዝህ ትሑታን ተገዥዎችና ከአንተም ጋር የምንቋረብ አምላኪ አገልጋዮች እንድታደርገን አንተን በመማፀን ላይ የምንገኝ አገልጋዮችህ ነን፡፡ አቤቱ አንተ ጌታችን ሆይ! እኛ ደካሞች ነን፣ አንተ ደግሞ ኃያሉ፣ ኃይል የተመላው ነህ እኛ ሕይወት አልባዎች ነን፡፡ አንተ ደግሞ ታላቁ ሕይወት ሰጪ መንፈስ ነህ፡፡ እኛ ችግረኞች ነን፡፡ አንተ ደግሞ በሕይወት አኗሪው ኃይል የተመላው ነህ፡፡ አቤቱ አንተ ጌታችን ሆይ! ፊቶቻችንን ምሕረት ወደተመላው ገጽታህ መልስልን፣ ከመንግስተ-ሰማያው የአንተ ገበታ የተትረፈረፈውን የአንተን ፀጋ መግበን በላቁት የአንተ መላእክት ሠራዊት እርዳን፣ በአብሃ መንግስትም ቅዱሳን አማካይነት አጠንክረን፡፡ በእውነቱ አንተ ቸሩ መሐሪው ነህ፡፡ አንተ የታላቅ በረከት ባለቤት ነህ በእርግጥም አንተ ሩኅሩኁና ጸጋ-የተመላው ነህና፣ጸጋ-የተመላው ነህና፡፡

bahaiprayers.net
Also in: bn en
~818w BH00568IMP
….. ኃጢአትንና በደልን በሰዎች ፊት መናዘዝ….. አይፈቀድም፡፡ ኃጢአተኛው በራሱና በአምላክ መካከል እንዲህ በማለት ከምሕረት ውቅያኖስ ምህረትን መማፀን ከቸርነትህም ሰማይ ይቅርታን መለመን አለበት፡፡
እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ! ለእኔም ለአባቴም ለእናቴም ይቅርባ ባይነትህን ትፈቅድልን ዘንድ በጣፋጭ ቃላትህ በጣም በመመሰጣቸው የክብር ከፍታ ቁንጮ ወደሆነው ፣ ወደ እጅግ በጣም ታላቅ ሰማዕትነት ስፍራ በፍጥነት በገሠገሡት በእውነተኞች አፍቃሪዎችህ ደም እማለድሃለሁ፤ በዕውቀትህ ውስጥ ተሸፍነው በሚገኙት ምስጢራትና በበረከትህ ውቅያኖስ ውስጥ በተቀመጡት ዕንቁዎችም እማፀንሃለሁ፡፡ ከእነዚያ ምሕረትን ከሚያሳዩት አንተ በእውነቱ ከሁሉም በላይ መሀሪው ነህ፡፡ ከአንተ ከዘለዓለም ይቅር ባዩ ፍጹም በረከት ከተመላው በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ጌታ ሆይ! ይህ የኃጢአተኛነት ሕልውና ወደ ልግስናህ ውቅያኖስ ፊቱን ሲመልስ፣ ይህም ደካማው የመለኮታዊ ኃይልህን መንግስት ሲመልስ ይህም ደካማው የመለኮታዊ ኃይልህን መንግስት ሲሻ ይህም ድሀው ፍጡር ራሱን ወደ ሀብትህ ቀኑ ኮከብ ሲያዘነብል ታየዋለህ፡፡ ጌታ ሆይ በምሕረትህና በፀጋህ እርሱ የለመነህን አትንሳው ከበረከትህም ግልፀቶች አትከልክለው፣ በሰማይህ ውስጥና በምድርህ ላይ ለሚኖሩት ሁሉ በሰፊው ከከፈትከው በርህም አታብርረው፡፡ እግዚኦ! እግዚኦ ኃጢአቶቼ ወደ ቅድስናህ መንበር ከመቅረብ ከልክለውኛል፤ በደሎቼም ከግርማ ሞገስህ ድንኳን በጣም ርቄ እንድጠጋ አድርገውኛል፡፡ አንተ እንዳላደርግ የከለከልከኝ አድርጌአለሁ፤ እንድፈጽመው ያዘዝከኝን አልፈፀምኩም፡፡ ወደ አንተ ለመቅረብ የሚያስችለኝን በበረከትህ ብዕር ትጽፍልኝ ዘንድ በኔና በይቅርባይነትህ በይቅርታህም መካከል ከተጋረጡት በደሎቼም ታነፃኝ ዘንድ፣ በእርሱ የስሞች ሉዓላዊ ጌታ በሆነው እለምንሃለሁ፡፡ በእውነቱ አንተ ምንም የማይሳነው በረከት የተመላው ነህና፡፡ ከአንተ ከኃያሉ፣ ፀጋ ከተመላው በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ጌታ አምላኬ ሆይ ፣ አንተ የተከበርክ ነህ ስለ አንተ ለማውሳት በሞከርኩ ቁጥር በከባድ ኃጢአቶቼና በአንተ ላይ በፈፀምኩአቸው አሳዛኝ በደሎቼ እገታለሁ፣ ከፀጋህም ሙሉ በሙሉ ተነፍ ጌ፣ የአንተን ምስጋና ለማወደስም ፍጹም ኃይል፣ አልባ ሆኜ እገኛለሁ፡፡ ሆኖም በፀጋህ ላይ ያለኝ ታላቅ እምነት፣ በአንተ ላይ ያለኝን ተስፋ ያድስልኛል፣ አንተ ቸርነት በተመላበት ሁኔታ እንደምትለግሰኝ ያለኝ እርግጠኝነትም እንዳወድስህና አንተ ያለህን ነገሮች ሁሉ ከአንተ እንድለምን ያደፋፍረኛል፡፡ አምላኬ ሆይ ልቤ ለክፋት የተጋለጠ ስለሆነ፣ ለራሴ እዳትተወኝ፣ በስሞችህ ውቅያኖሶች የሰጠሙት ሁሉ በሚመሠክሩለት፣ ከተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ ብዛት አልፎ በሚገኘው ምሕረትህ እማፀንሃለሁ፡፡ ስለዚህ በመከላከያህ ምሽግና በእንክብካቤህ መጠለያ ውስጥ ጠብቀኝ፣ አምላኬ ሆይ፣ እኔ ብቸኛ ፍላጎቱ አንተ በኃያልነትህ ስልጣን የወሰንከው የሆነው ነኝ፤ እኔ ለራሴ የመረጥኩት ፀጋ በተመላበት ትዕዛዝህና በፈቃድህ ውሳኔ ለመደገፍ፣ በድንጌጌህና በፍርድህ ምልክቶችም እንድታገዝ ብቻ ነው፡፡ አቤቱ አንተ የእነዚያ አንተን የሚናፍቁት ልቦች ተወዳጅ የሆንከው ሆይ፣ ወደ አንተ ቅዱስ መንበር፣ ወደ አንተ ደጀሰላምና ወደ አንተ ቤተ-መቅደስ ከመቅረብ እንዳትነፍገኝ፣ በእምነትህ ክስተቶ በዕውቀት-ብልጭታህም ንጋቶች በግርማህም መገለጫዎች ፣በዕውቀትህም ግምጃ ቤቶች እማፀንሃለሁ፤ ጌታዬ ሆይ ወደ እርሱ ቅዱስ መንበር እንድደርስ፣ በእርሱም ስብዕና ዙሪያ እንድዞር፣ በእርሱም ደጃፍ ፊት በትህትና እንድቆም እርዳኝ፡፡ አንተ ስልጣኑ ከእምቅድመ-ዓለም እስከ ዘለዓለም የሚኖረው ነህ፡፡ ምንም ነገር ከዕውቀትህ አያመልጥም፡፡ አንተ በእውነቱ የስልጣን አምላክ የክብርና የጥበብ አምላክ ነህ፡፡ የዓለማት ሁሉ ጌታ የሆነው፣ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን፡፡ አቤቱ አንተ አምላኬና የሁሉ ነገሮች አምላክ፣ ክብሬና የሁሉ ነገሮች ክብር፣ ፍላጎቴና የሁሉ ነገሮች ፍላጎት ብርታቴና የሁሉ ነገሮች ብርታት፣ ንጉሴና የሁሉ ነገሮች ንጉስ-ጌታዬና የሁሉ ነገሮች ባለቤት ዓላማዬና የሁሉ ነገሮች ዓላማ፣ አንቀሳቃሼና የሁሉ ነገሮች አንቀሳቃሽ የሆንከው ጌታ ሆይ፣ ስምህ የተወደሰ ይሁን! ከፍቅራዊ ምሕረቶችህ ውቅያኖስ እንድከለከል፣ ከቅርበትህ ዳርቻዎችም እንድርቅ እንዳታደርገኝ እማጠንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ፣ ከአንተ በቀር ሌላ ማንኛውም ነገር አይጠቅመኝም፣ ወደ አንተ በቀር ወደ ማንም መቅረቡም ምንም አይረዳኝም፣ ከእነዚያ ፊቶቻቸውን ወደ አንተ አቅጣጫ ከአቀኑትና፣ አንተን ለማገልገል ከተነሱት ጋር እንድትቆጥረኝ፣ ከአንተ ከራስህ በስተቀር ማንኛውም ነገር እንዳያስፈልግህ በአደረግህባቸው ሀብቶቻችህ ብዛት እማጠንሃለሁ፡፡ እንግዲህ ጌታዬ ሆይ አገልጋዮችህንና ሴት አገልጋዮችህን ይቅር በላቸው፡፡ በእውነቱ አንተ ምንጊዜም ይቅር ባዩ ከሁሉም በላይ ሩኅሩኁ ነህና፡፡ ጌታ ሆይ፤ ምስጋና ለአንተ ይሁን ኃጢአታችንን ቅር በለን፣ በእኛ ላይ ምሕረት ይኑርህ፡፡ ወደ አንተም ለመመለስ አስቸለን፡፡ በአንተ ላይ በቀር በሌላ በምንም ላይ እንዳንተማመን አድርገን በፀጋህ አማካይነት፣ ያንን አንተ የምትወደውንና የምትሻውን ከአንት በጣም የሚጠበቀውን ስጠን፡፡ የእነዚያን በእውነት ያመኑትን ደረጃ ከፍ አድርግ ፀጋ በተመላበት ይቅር ባይነትህም ይቅር በላቸው በእውነቱ አንተ በአደጋ ጊዜ ረዳቱ በገዛ ራሱም ነዋሪው ነህና፤ ጌታዬ ሆይ አቤቱ አንተ የጌቶች ጌታ እርሱ ተፈላጊውን የሚሰጠውና በሮቹን ሁሉ የሚከፍተው የሆንከው ሆይ የአንተን ስም ለማንሳት በቀር ለእያንዳንዱ ሌላ ስም ማንሳት ለአንተ ውዳሴም በቀር ለእያንዳንዱ ሌላ ውዳሴ በቅርበትህ ምክንያት ከተደሰትኩት ደስታም በቀር ለእያንዳንዱ ሌላ ደስታ፣ ከአንተ ጋር በመቋረብ ምክንያት ለአገኘሁት እርካታም በቀር ለእያንዳንዱ ሌላ እርካታ ለፍቅርህና ለመልካም ደስታህም ሐሴት በቀር ለእያንዳንዱ ሌላ ሐሴት ከአንተ ጋር ምንም ግንኙነት ለሌላቸው ከእኔ ጋር ግንኙነት ለነበራቸው ነገሮች ሁሉ ቅርታ እንድታደርግልኝ እለምንሃለሁ፡፡ አቤቱ አንተ ፍጹም ኃያል አምላክ ሆይ ! እኔ ኃጢአተኛ ነኝ፣ አንተ ግን ይቅርባይ ነህ! እኔ ጥፋቴ የበዛ ነው፣ አንተ ግን ሩኅሩህ ነህ፣ እኔ በስሕተት ጨለማ ውስጥ ነኝ፣ አንተ ግን የምህረት ብርሃን ነህ! አቤቱ አንተ ለጋሥ አምላክ ሆይ! ኃጢአቴን ይቅር በለኝ፣ በረከትህን አውርድልኝ፣ ስሕተቴን አትመልከት፣ መጠለያ ስጠኝ በትዕግስትህ ምንጭ ውስጥ አስጥመኝ፣ ከማናቸውም ደቄና በሽታም ፈውሰኝ፡፡ አንፃኝ ቀድሰኝ፣ ኃዘንና ትካዜ እንዲጠፉ፣ ፍስሐና ሐሴት እንዲወርዱ፣ ከሚጎርፈው ቅድስናህ አካፍለኝ፡፡ ጭንቀትና ተስፋ ማጣት በደስታና በታማኝነት እንዲለወጡ አድርግልኝ፣ በፍርሐትም ፈንታ ልበ ሙሉነት እንዳገኝ ፈቃድህ ይሁን፡፡ በእውነቱ አንተ ይቅር-ባዩ- ሩኅሩኁ ለጋሱና ተወዳጁ ነህና፡፡ አምላኬ ሆይ! በጭካኔያቸው፣ በተሳሳተ ስራቸውና በሚያደርጉት ተንኮል ሁሉ የዋሃን በመሆናቸው የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር ትላቸው ዘንድ በአፌም በልቤም እለምንሃለሁ፡፡ ክፉውን ከደጉ፣ ስሕተቱን ከትክክለኛው፣ፍትሕን ከፍርድ ማጓደል ለይተው ሳያውቁ የራሳቸውን ፍላጎት ያደርጋሉ፡፡ ከእነርሱ መካከል በጣም የተሳሳተውን ሰው ይከተላሉ፤ አምላክ ሆይ ምህረትን አውርድላቸው፣ በዚህ በችግር ዘመን ከመከራ ሁሉ ጠብቃቸው፡፡ ይህ ሁሉ መከራና ችግር ለዚህ በጨለማ ጉድጓድ ለተጣለው አገልጋይህ ይሆን ዘንድ ፈቃድህ ይሁን፡፡ ማናቸውንም ኃዘን ሁሉ ለእኔ አድርገው፡፡ ለተወዳጆችህም ሁሉ መስዋዕት ለመሆን እብቃኝ ለታላቅነትህ ወሰን የሌለው አምላክ ሆይ፣ ነፍሴ ህይወቴ መላው ሰውነቴ፣ መንፈሴም ስለ እነርሱ መስዋዕት ይሆን ዘንድ ፈቃድህ ይሁን፤ አምላኬ ሆይ የበደሉኝን፣ ያደሙብኝንና ፍርድንም ያጓደሉብኝን ሁሉ ይቅር እንድትላቸው፣ እኔ ዝቅተኛው አገልጋይህ በግንባሬ ተደፍቼ እለምንሃለሁ፡፡ መልካም ችሮታህን ናቸው፣ ደስታን ስጣቸው ከኃዘን አድነህ ሰላምንና ብልጽግናን አድላች፣ ታላቅ ደስታን ስጣቸው፤ በረከትህንም አውርድላቸው፤ አንተ ራሱን ችሎ ነዋሪው ኃያሉ፣ በአደጋ ጊዜም ረዳቱ ነህና፤
bahaiprayers.net
Also in: bs en pt ro ur
~908w BH08242
  • Education

ጌታ አምላኬ ሆይ፤ ምስጋና ለአንተ ይሁን! ማንም ሰው በሚገባ ባላወቀው፣ ታላቅነቱንም ማንም ነፍስ ባልተረዳው ስምህ እማፀናሀለሁ፤ ልቤን የፍቅርህና የትውስታህ ማኅደር እንድታደርግልኝ፣ በእርሱ የግልፀትህ ምንጭና የምልክቶችህ ጎሕ በሆነው እማፀንሃለሁ፡፡ እንዲሁም ከዚህ ከልቤ የጥበብህ የህይወት ውሃዎች፣ የውዳሴህና የምስጋናህ ንጹህ ጅረቶች ይወርዱ ዘንድ ከታላቁ ውቅያኖስህ ጋር አገናኘው፡፡ የአካሌ መለያልዮች ስለአንድነትህ ይመሠክራሉ፤ የእራሴ ፀጉርም ስለሉዓላዊትህና ስለታላቅነትህ ኃይል ያውጃል፡፡ ራሴን ፍጹም ዝቅ በማድረግና ሙሉ በሙሉ በመርሳት በፀጋህ በር ላይ ቆሜአለሁ፣ በቸርነትህም ካባ ጠርዝ ላይ ተጠንላጥያለሁ፤ የዓይኖቼንም እይታ ወደ ስጦታዎችህ አድማስ መልሼአለሁ፡፡ አምላኬ ሆይ ለግርማህ ታላቅነት የሚገባውን ዕድል ወስንልኝ ሙታንም ከመቃብሮቻቸው በፍጥነት በመውጣትና እምነታቸውን ሙሉ በሙሉ በአንተ ላይ በመጣል፣ የእይታቸውንም ትኩረት ወደ እምነትህ አቅጣጫና ወደ ግልፀትህ የንጋት ሥፍራ በመመለስ ወደ አንተ በፍጥነት እንዲለግሱ እምነትህን እንዳስተምር፣ በሚያጠናክረው ፀጋህ እርዳኝ፤ አንተ በእውነቱ ፍጹም ÷ ኃይል የተመላው÷ ፍጹም ከፍተኛው ሁሉን አዋቂው ፍጹም ጠቢቡ ነህና፤ አምላክ ሆይ! የአገልጋዮችህ ጉዳይ ሁሉ እንዲሰምር ከተሞችህም እንዲያብቡ ለማድረግ እንድንችል ትረዳኝ ዘንድ፣ከሁሉም በላይ በተከበረው ስምህ እለምንሃለሁ፡፡ አንተ በአውነቱ በሁሉም ነገሮች ላይ ስልጣን ያለህ ነህና፡፡ አቤቱ አንተ እጅግ ተዋጄ ሆይ! በሕግ ተላላፊዎች ከባድ ወረራም ሆነ በከሃዲዎች ቁጣ በማናውላውልበት ሁኔታ ስምህን ከፍ ከፍ ለማድረግ መልዕክትህን ለማስተላለፍና እምነትህን ለማወጅ እንድንችል እኔንም አገልጋዮችህንም በፀጋህ እንድትረዳን ÷ ሰላም ማጣትን ወደ እርጋታ፣ ፍርሐትን ወደ ልበ ሙሉነት÷ ድክመትን ወደ ብርታት÷ ውርደትንም ወደ ክብር በምትለውጥበት ስምህ እማፀንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ! እኔ ወደ አንተ ጥሪ ያዳመጥኩ÷ ወደ አንተም ለመቅረብ የፈጠርኩ÷ ከራሴም በመሸሽ ልቤን በአንተ ላይ ያሳረፍኩ ሴት አገልጋይህ ነኝ፡፡ ጌታዬ ሆይ÷ ከእነዚያ በአንተ ባላመኑትና የአንተን እውነት በአስተባበሉት ሰዎች በተዘዋዋሪ መንገድ ከሚሰነዝረው ሃሳብ እንድትመክተኝ÷ ከውስጡ የምድር ሀብቶች ሁሉ እንዲመጡ በተደረጉበት ስምህ እማፀንሃለሁ፡፡ አንተ የሚያስደስትህን ለማድረግ ኃይል የተመላው ነህ፡፡ አንተ በእውነቱ ሁሉን አዋቂው ፍጹም ጠቢቡ ነህ፡፡ ተወዳዳሪ ሌለህ አምላክ ሆይ! አቤቱ አንተ የመንግስቱ ጌታ! እነዚህ ነፍሶች መንግስተ ሰማያዊ ሠራዊትህ ናቸው፡፡ እያንዳንዳቸው እንደ አንድ ጦር ኃይል በመሆን በእግዚአብሔር ፍቅርና በመለኮታዊ ትምህርት ውጋገን እነዚህን ሀገሮች ያስገብሩ ዘንድ በከፍተኛው የሰማይ ሠራዊት ቡድኖች እርዳቸው፡፡ አምላክ ሆይ! ድጋፍና እርዳታ ሁንላቸው በመንግስትህ ኃይልና በመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ ድምፃቸውን ያሰሙ ዘንድ በምድረ በዳ፣ በተራራ፣ በሸለቆ፣ በጥሻ፣ በሜዳና በባህር አለኝታ ሁናቸወው፡፡ በእውነቱ አንተ፣ ኃይል የተመላው፣ ኃያሉና ምንም የማይሳነው ነህና፣ እንዲሁም አንተ ጠቢቡ ሁሉን ሰሚውና የሚያየው ነህና፡፡ አምላኬ ሆይ! አምላክ ሆይ ! ይሀ ከንፈ ሰባራ ወፍነው በረራውም በጣም ዝግተኛ ነው፣ ወደ ብልጽግናና ወደ መዳን ከፍታ ጫፍ ለመብረር እንዲችል፣ በከፍተኛ ሐሴትና ደስታ ወሰን በሌለው ሕዋ ስፋት ውስጥ እንዲከንፍ፣ በላቀው ስምህ በሁሉም አካባቢዎች ዜማውን እንዲያሰማ፣ በዚህም ጥሪ ጆሮዎችን እንዲያስደስት፣ አይኖችም የመርሖን ምልክቶች በማየት እንዲበሩ እንዲያደግ እርዳው! ጌታ ሆይ! እኔ ረዳት የሌለኝ፣ ብቸኛና ዝቅተኛ ነኝ፡፡ ለእኔ ከአንተ በስተቀር ሌላ ደጋፊ፣ ከአንተ በስተቀር ሌላ ደጋፊ፣ ከአንተ በስተቀር ሌላ ረዳት፣ ከአንተም ሌላ የሚያኖረኝ የለም፡፡ ለአገልግሎትህ አጠናክረኝ፣ በመላእክትህ ሠራዊት እርዳኝ፣ ቃልህን በማሰራጨት ተግባሬ ድልን አጎናጽፈኝ፣ በፍጡራንም መካከል የአንተን ጥበብ እንድለፍፍ አድርገኝ፡፡ በእውነቱ፣ አንተ ለደካሞች ረዳቱ፣ በዝቅተኞችም ተከላካዩ ነህና፣ በእውነቱም አንተ ኃይል የተመላው፣ ኃያሉና የማይገታው ነህና! እግዚአብሔር ምላኬ ሆይ! ድቅድቅ ጨለማ አካባቢዎችን ሁሉ መክበቡን፣ ሀገሮችም ሁሉ በሀሳብ ቅራኔ ሰደድ እሳት እየጋዩ መሆናቸውን፣ እንዲሁም በምድር ምስራቆችና በምዕራቦችዋ ሁሉ እንዴት የጦርነትና የእልቂት እሳት እንደተቀጣጠለ አንተ ታያለህ፡፡ ደሙ እጎረፈ ነው፤ አስከሬኖችም በመሬት ላይ ተዘርረዋል፣ የተቀሉ ጭንቅላቶችም በጦራ ሜዳ አቧራ ላይ ተጥለዋል፡፡ ጌታ ሆይ! በእነዚህ ደናቁርት ላይ ኃዘኔታ ይኑርህ፣ በምህረትና በይቅርታ አይንም ተመልከታቸው እነዚህ አድማሱን የሸፈኑት ጥልቅ ደመናዎች ይበተኑ ዘነድ፣ የእውነት ፀሐይ በዕርቅ ጨረሮች ይበራ ዘንድ፣ ይህ ጥልቅ ጨለማ ይወገድ ዘንድ፣ የሰላም ደማቅ ብርሃንም ጮራውን በሁሉም አገሮች ላይ ይፈነጥቅ ዘንድ ይህን እሳት አጥፋው፡፡ ጌታ ሆይ! ህዝቦችን ከጥላቻና ከጠላትነት ውቅያኖስ አዘቅት አውጣቸው፣ ከዚያም ከማይበገረው ጨለማ አድናቸው፡፡ ልቦቻቸውን አስተሳሰር፣ አይኖቻቸውንም በሰላምና በእርቅ ብርሃን አብራ፤ ከጦርነትና ከደም መፍሰስ አዘቅት አድናቸው፣ ከስህተት ጨለማም ነፃ አውጣቸው፣ ግርዶሹን ከዓይኖቻቸው ግለጥላቸው፣ ልቦቻቸውንም በመርሖ ብርሃን አብራ፤ በአዛኝ ምህረትህና ርኅራሄህ ያዛቸው እንጂ፣ የኃያሎቹን ቅልጥሞች እንኳ በሚያንቀጠቅጠው በአንተ ፍትህና በቁጣህ አትፍረድባቸው፤ ጌታ ሆይ! ጦርነቶች ተራዝመዋል፡፡ ጭንቀትና ሥጋት ተባብሰዋል፤ እንዳንዱም ለምለም አካባቢ ወደ ጠፍነት ተለውጧል፡፡ ጌታ ሆይ! ልቦች አዝነዋል፣ ነፍሶችም ተጨንቀዋል፡፡ በእነዚህ ምስኪኖች ነፍሶች ላይ ምሕረት ይኑርህ እንጂ ራሳቸው ለሚመኙት ከመጠን ያለፈ ፍላጎት አትተዋቸው፡፡ ጌታ ሆይ! ፎቶቻቸው በመርሐ ጨረር የበሩ፣ ከዓለም የተላቀቁ፣ስምህን የሚያወድሱ፣ የአንተን ምስጋና የሚናገሩ፣ በሰውም ዘር መካከል የቅዱስነትህን መዓዛ የሚያሰራጩ ትሑታንና ታዛዦች ነፍሶችን በአገሮችህ ሁሉ ውስጥ አስነሣ፡፡ ጌታ ሆይ! ጀርባዎቻቸውን አጠንክር፣ሽንጦቻቸውን ደግፍ፤ ከሁሉም በላይ ታላቅ በሆኑት በፍቅርህ ምልክቶችም ልቦቻቸውን አስደስት፡፡ ጌታ ሆይ! በእውነቱ እነርሱ ደካሞች ናቸው፤ አንተ ግን ብርቱውና ኃያሉ ነህ፣ እነርሱ አቅመቢሶች ናቸው፤ አንተ ግን ረዳቱና መሐሪው ነህ፤ ጌታ ሆይ! የአመጽ ውቅያኖስ እየሞገደ ነው፤ ሁሉንም አካባቢዎች ባቀፈው ወሰን በሌላው ፀጋህ በስተቀር እነዚህ ኃይለኛ ነፋሶች አይረጉም፤
ጌታ ሆይ ! በእውነቱ ህዝቦች በከፍተኛ መድራዊ ምኖት አዘቅት ውስጥ ናቸው፤ ወሰን ከሌለው ልግስናህም በስተቀር ምንም ነገር ሊያድናቸው አይችልም፡፡
ጌታ ሆይ! የእነዚህን የእርኩስ ምኞቶች ጨለማ አስወግድ፣ ሀገሮችም ሁሉ በቅርብ ጊዜ በሚበሩበት በፍቅርህ ፋኖስ ልቦችን አብራ፡፡ እነዚያን፣ ለውበትህ ፍቅር ሲሉ፣ አገሮቻቸውን ቤተሰቦቻቸውንና ልጆቻቸውን ጥለው፣ መዓዛዎችህን ለማሰራጨትና ትምህርቶችህን ለማስፋፋት ፣ ወደ ውጭ አገሮች የሚጓዙትን ተወዳዶችህን አጠንክራቸው፤ በብቸኝነት ጊዜአቸው ጓደኛ፣ በባዕድ አገር ረዳታቸው፣ የኀዘናቸው አስወጋጅ፣ በመከራ ጊዜ አጽናኝ፤ ሁንላቸው፤ ለጥማታቸው የሚያረካ መጠጥ፣ ለበሽታቸው ፈዋሽ መድኃኒት፣ የልቦቻቸው ስሜት ነበልባል አብራጅ ቅባት ሁን፤ በእውነቱ፣ አንተ ከሁሉም በላይ ለጋሱ፣ ወሰን የሌለው ፀጋ ባለቤት ነህ፣ እንዲሁም አንተ ሩኅሩኁና መሐሪው ነህና፡፡ አቤቱ አንተ ቸር ጌታ ሆይ ! የመርሖን አውራ ጎዳና ስለአሳየኽን፣ የመንግስትህን በሮች ስለከፈትክልንና ራስህንም በእውነት ፀሐይ አማካይነት ስለከሰትክልን ምስጋና ለአንተ ይሁን፤ ለዕውራን ማየትን ሰጥተሃል፣ ለደንቆሮዎች መስማትን አድለሃል፤ ሙታንን አስነስተሃል፣ ድሆችን አበልጽገሃል፣ መንገድ የሳትቱን መንገዱን አሳይተሃቸዋል፣ እነዚያን ከንፈሮቻቸው ደቁትን ወደ መርሐ ምንጭ መርተሃቸዋል፣ የተጠቀሙትንም ዓሶች ወደ እውነት ውቅያኖስ እንደደርሱ አድርገሃል፣ የሚንከራተቱትንም ወፎች ወደ ፀጋ የጽጌረዳ አትክልት ሥፍራ ጋብዘሃል፡፡ አቤቱ አንተ ፍጹም ኃያል ሆይ! እኛ ባሮችህና ምስኪኖችህ ነን፤ እሩቅ ነንና የአንተን ቅርበት እንሻለን፣ ለምንጭህም ውሃ እንጠማለን፣ ሕሙማን ነንና ፈውስህን እንናፍቃለን፡፡ በመንገድህ እንጓዛለን፣ ነፍሶች ሁሉ አምላክ ሆይ ወደ ቀጥተኛው መንገድ ምራን የሚለውን ጩኽት ያሰሙ ዘንድ፣ መዓዛህን ከማሰራጨት በስተቀር ሌላ ዓላማና ተስፋ የለንም፡፡ ብርሃኑን ለማየት አይኖቻቸው እንዲከፈቱ፣ ከድንቁርና ጨለማ ነፃ እንዲወጡ፣ በመሪነትህም ፋኖስ ዙሪያ እንዲሰባሰቡ፣ ቁራሽ ቢሾች ድርሻቸውን እንዲቀበሉ፣ የተገለሉትም ሁሉ የምሥጢሮችህ ተካፋዮች እንዲሆኑ ፈቃህ ይሁን፡፡ ፍጹም ኃያል ሆይ! በምሕረትህ አስተያየት ተመልክተን፤ መንግስተ ሰማያዊ ማረጋገጫን አድለን፡፡ ለአገልግሎትህ እንዲረዳንና እንደ አንፀባራቂ ከዋክብት የምሖህን ብርሃን በእነዚህ ክፍለ ሀገሮች እንድናበራ የመንፈስ ቅዱስን እስትንፋስ አጎናጽፈን፤ አንተ በእርግጥም ብርቱው፣ ኃያሉ ጠቢቡና የሚያየው ነህና፤

bahaiprayers.net